የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የፖሊሲው ትግበራ ግብርናውን በማዘመን ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የላቀ ነው

Mar 13, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ) :-አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ትግበራ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የላቀ መሆኑ ተገለጸ።

ፖሊሲውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማስተዋወቅን ዓላማ ያደረገ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እና የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ በተገኙበት በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡


በዚህ ወቅት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር እንዳመለከቱት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም ዘርፎች በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ተችሏል፡፡

በዘርፉ እየተመዘገበ ያለውን ውጤት ለማጠናከርና የላቀ እመርታ ለማስመዝገብ እንደ አገር የተቀረጸው አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ፖሊሲው ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳ የላቀ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026