
ቡታጅራ ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ) :-አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ትግበራ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የላቀ መሆኑ ተገለጸ።
ፖሊሲውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማስተዋወቅን ዓላማ ያደረገ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እና የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ በተገኙበት በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

በዚህ ወቅት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር እንዳመለከቱት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም ዘርፎች በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በዘርፉ እየተመዘገበ ያለውን ውጤት ለማጠናከርና የላቀ እመርታ ለማስመዝገብ እንደ አገር የተቀረጸው አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ፖሊሲው ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳ የላቀ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ነው፡፡
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026