
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- የልማት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ገቢ ለማሟላት ዘርፉን በቴክኖሎጂ መደገፍና የህዝቡን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ ገለጹ።
ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የመጡ የታክስ አመራሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም(አይ ኤም ኤፍ) እና የዓለም ባንክ ተወካዮች በተገኙበት ለሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብ ላይ ያተኮረው ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል፡፡

ከጉባኤው መጠናቀቅ በኋላ ተሳታፊዎች የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልና የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጨምሮ በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ የመካከለኛ ዘመን የገቢ አሰባሰብ ስትራቴጂ የቀረጹና ወደ ስራ የገቡ ሀገራት ውጤታማ መሆን ችለዋል።
ኢትዮጵያ የገቢ መሰብሰብ አቅሟን ለማሳደግ በተያዘው ዓመት የመካከለኛ ዘመን የገቢ አሰባሰብ ስትራቴጂ ቀርጻ ወደ ስራ ገብታለች ብለዋል።
የልማት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ገቢ ለማሟላት ዘርፉን በቴክኖሎጂ መደገፍና የህዝብን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

ጉባኤው በሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችና የመፍትሔ ርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል የልምድ ልውውጥ መደረጉንም አንስተዋል፡፡

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ክላራ ሚራ የአፍሪካ ሀገራት በገቢ አሰባሰብ ሂደት መሻሻል እያሳዩ ቢሆንም ካለው አህጉራዊ አቅም አንፃር የሚሰበሰበው ገቢ በቂ አይደለም ብለዋል፡፡
በመሆኑም ተቋሙ የሀገራቱን የውስጥ ገቢ አሰባሰብ አቅም ለማሳደግ የሚያደረገውን የቴክኒክና ሙያዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

በማላዊ ገቢዎች ሚኒስቴር የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ምክትል ዳይሬክተር ማሳ ሳማንታ ኢትዮጵያ በራሷ የገቢ አቅም ትልልቅ የልማት ሥራዎችን እያከናወነች መሆኑን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች አበረታችና ልምድ ሊወሰድባቸው የሚገባቸው መሆናቸውን ገልጸው፤ ይህም ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር የጎላ አበርክቶ ይኖራቸዋል ነው ያሉት፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026