የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

አድናቆት የተቸረው ታዳጊዎችን በፈጠራና ቴክኖሎጂ የማበልጸግ ጥረት

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 06/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታዳጊዎችን በፈጠራና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ለማብቃት ያላትን ቁርጠኝነት የአሜሪካ ኤምባሲ አደነቀ።

አሜሪካ የመጪው ዘመን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ መሪ ለሚሆኑት አፍሪካውያን ወጣቶች ድጋፍ እያደረገች መሆኗንም ጠቁመዋል።

በአሜሪካ ኤምባሲ የባህል ጉዳዮች ምክትል ኃላፊና በኢትዮጵያ የስፔስ ማዕከላት ዳይሬክተር ስትዋርት ዴቪስ እንደገለጹት፤ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ሂሳብ(ስቴም) አሜሪካ ድጋፍ ከምታደርግባቸው ዘርፎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።

በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ባሉ ስድስት የ'ስቴም' ማዕከላት በ'ስቴም'፣ ሮቦቲክስና ሌሎች ቴክኖሎጂ ዘርፎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።


የስቴም ማዕከላቱን ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በመቀሌ፣ ድሬዳዋና ጅማ መኖራቸውን ጠቁመው፤ በሃዋሳ ተጨማሪ ማዕከል ለመክፈት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሮቦቲክስ፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች የፈጠራ ሃሳቦችን ለማበልፀግ የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውን አድንቀዋል።

በየጊዜው ወደ ማዕከላቱ የሚመጡ ታዳጊ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህም ታዳጊዎቹ ለመማርና ለመሻሻል ያላቸውን ፍላጎት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ የሳይንስ ሙዚየምን ጨምሮ የታዳጊዎችን የፈጠራና ቴክኖሎጂ እውቀት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ለዘርፉ ማደግ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

አሜሪካም አፍሪካውያን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም እንዲያወጡ ለማድረግ እገዛ እያደረገች መሆኗን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.