
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 06/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታዳጊዎችን በፈጠራና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ለማብቃት ያላትን ቁርጠኝነት የአሜሪካ ኤምባሲ አደነቀ።
አሜሪካ የመጪው ዘመን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ መሪ ለሚሆኑት አፍሪካውያን ወጣቶች ድጋፍ እያደረገች መሆኗንም ጠቁመዋል።
በአሜሪካ ኤምባሲ የባህል ጉዳዮች ምክትል ኃላፊና በኢትዮጵያ የስፔስ ማዕከላት ዳይሬክተር ስትዋርት ዴቪስ እንደገለጹት፤ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ሂሳብ(ስቴም) አሜሪካ ድጋፍ ከምታደርግባቸው ዘርፎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።
በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ባሉ ስድስት የ'ስቴም' ማዕከላት በ'ስቴም'፣ ሮቦቲክስና ሌሎች ቴክኖሎጂ ዘርፎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።

የስቴም ማዕከላቱን ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በመቀሌ፣ ድሬዳዋና ጅማ መኖራቸውን ጠቁመው፤ በሃዋሳ ተጨማሪ ማዕከል ለመክፈት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሮቦቲክስ፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች የፈጠራ ሃሳቦችን ለማበልፀግ የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውን አድንቀዋል።
በየጊዜው ወደ ማዕከላቱ የሚመጡ ታዳጊ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህም ታዳጊዎቹ ለመማርና ለመሻሻል ያላቸውን ፍላጎት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የሳይንስ ሙዚየምን ጨምሮ የታዳጊዎችን የፈጠራና ቴክኖሎጂ እውቀት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ለዘርፉ ማደግ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
አሜሪካም አፍሪካውያን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም እንዲያወጡ ለማድረግ እገዛ እያደረገች መሆኗን ጠቁመዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026