
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 06/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታዳጊዎችን በፈጠራና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ለማብቃት ያላትን ቁርጠኝነት የአሜሪካ ኤምባሲ አደነቀ።
አሜሪካ የመጪው ዘመን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ መሪ ለሚሆኑት አፍሪካውያን ወጣቶች ድጋፍ እያደረገች መሆኗንም ጠቁመዋል።
በአሜሪካ ኤምባሲ የባህል ጉዳዮች ምክትል ኃላፊና በኢትዮጵያ የስፔስ ማዕከላት ዳይሬክተር ስትዋርት ዴቪስ እንደገለጹት፤ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ሂሳብ(ስቴም) አሜሪካ ድጋፍ ከምታደርግባቸው ዘርፎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።
በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ባሉ ስድስት የ'ስቴም' ማዕከላት በ'ስቴም'፣ ሮቦቲክስና ሌሎች ቴክኖሎጂ ዘርፎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።

የስቴም ማዕከላቱን ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በመቀሌ፣ ድሬዳዋና ጅማ መኖራቸውን ጠቁመው፤ በሃዋሳ ተጨማሪ ማዕከል ለመክፈት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሮቦቲክስ፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች የፈጠራ ሃሳቦችን ለማበልፀግ የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውን አድንቀዋል።
በየጊዜው ወደ ማዕከላቱ የሚመጡ ታዳጊ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህም ታዳጊዎቹ ለመማርና ለመሻሻል ያላቸውን ፍላጎት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የሳይንስ ሙዚየምን ጨምሮ የታዳጊዎችን የፈጠራና ቴክኖሎጂ እውቀት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ለዘርፉ ማደግ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
አሜሪካም አፍሪካውያን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም እንዲያወጡ ለማድረግ እገዛ እያደረገች መሆኗን ጠቁመዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026