
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የንግዱ ማህበረሰብ መንግሥት የፈጠረውን ምቹ ዕድል እና እምቅ የመልማት አቅም በመጠቀም የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት ማሳደግ እንደሚገባው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
14ኛው የኢትዮ-ቻምበር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒት ግቡን በመምታት በስኬት መጠናቀቁን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና መርሀ ግብር ተካሂዷል።
የንግድ ትርዒቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን 300 የሚደርሱ የሀገራትና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ተሳትፈውበታል።

ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ 14ኛው የኢትዮ-ቻምበር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒት ግቡን በመምታት በስኬት ተጠናቋል።
የንግድ ትርዒቱ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ማስተዋወቅና ግብይት በመፈጸም በኩል ስኬታማ እንደነበርም አንስተዋል።
ከዚህም ባለፈ የንግድ ትርዒቱ የኢትዮጵያን ልክና መጠን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ መግለጥ የሚያስችል አውድ ፈጥሯል ነው ያሉት።

አያይዘውም ሚኒስቴሩ የንግዱን ማህበረሰብ የንግድ ፈቃድ በበይነ መረብ(ኦንላይን) በማደስና አዲስ በማውጣት ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስምንት ወራት 2 ነጥብ 3 ሚሊየን አዳዲስ ፈቃድ ማውጣት እና የእድሳት አገልግሎቶች መሰጠታቸውን ገልጸዋል።
ይህም ባለፉት ዓመታት ሲሰጥ ከነበረው አገልግሎት አንፃር በእጅጉ መሻሻሉን ገልጸው፣ ለንግዱ ማህበረሰብ የሚሰጠውን አገልግሎት የበለጠ ለማሳለጥ አበክረን እንሰራለን ብለዋል።

መንግስት የውጭ ምንዛሬ ግኝቱን ለማሳደግ በወሰዳቸው የፖሊሲ እርምጃዎች ውጤት መገኘቱን ጠቅሰው፣ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስምንት ወራት ከምርት ኤክስፖርት ብቻ 4 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር መገኘቱን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በአዲስ ከተደራጀ በኋላ ተስፋ ሰጭ ውጤት ቢያስመዘግብም ኢትዮጵያ ካላት አቅም አንፃር ከዚህ በላይ መስራት ይገባዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ ቀነኒሳ ለሚ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮ ቻምበር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒት የንግዱን ማህበረሰብ ተሳትፎ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በተለይም ከለውጡ በኋላ በተደረጉ የፖሊሲና የአስተዳደር እርምጃዎች የግሉ ዘርፍ መነቃቃት አሳይቷል ብለዋል።
በመካከለኛና አነስተኛ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑንም ገልጸዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026