
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የንግዱ ማህበረሰብ መንግሥት የፈጠረውን ምቹ ዕድል እና እምቅ የመልማት አቅም በመጠቀም የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት ማሳደግ እንደሚገባው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
14ኛው የኢትዮ-ቻምበር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒት ግቡን በመምታት በስኬት መጠናቀቁን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና መርሀ ግብር ተካሂዷል።
የንግድ ትርዒቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን 300 የሚደርሱ የሀገራትና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ተሳትፈውበታል።

ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ 14ኛው የኢትዮ-ቻምበር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒት ግቡን በመምታት በስኬት ተጠናቋል።
የንግድ ትርዒቱ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ማስተዋወቅና ግብይት በመፈጸም በኩል ስኬታማ እንደነበርም አንስተዋል።
ከዚህም ባለፈ የንግድ ትርዒቱ የኢትዮጵያን ልክና መጠን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ መግለጥ የሚያስችል አውድ ፈጥሯል ነው ያሉት።

አያይዘውም ሚኒስቴሩ የንግዱን ማህበረሰብ የንግድ ፈቃድ በበይነ መረብ(ኦንላይን) በማደስና አዲስ በማውጣት ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስምንት ወራት 2 ነጥብ 3 ሚሊየን አዳዲስ ፈቃድ ማውጣት እና የእድሳት አገልግሎቶች መሰጠታቸውን ገልጸዋል።
ይህም ባለፉት ዓመታት ሲሰጥ ከነበረው አገልግሎት አንፃር በእጅጉ መሻሻሉን ገልጸው፣ ለንግዱ ማህበረሰብ የሚሰጠውን አገልግሎት የበለጠ ለማሳለጥ አበክረን እንሰራለን ብለዋል።

መንግስት የውጭ ምንዛሬ ግኝቱን ለማሳደግ በወሰዳቸው የፖሊሲ እርምጃዎች ውጤት መገኘቱን ጠቅሰው፣ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስምንት ወራት ከምርት ኤክስፖርት ብቻ 4 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር መገኘቱን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በአዲስ ከተደራጀ በኋላ ተስፋ ሰጭ ውጤት ቢያስመዘግብም ኢትዮጵያ ካላት አቅም አንፃር ከዚህ በላይ መስራት ይገባዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ ቀነኒሳ ለሚ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮ ቻምበር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒት የንግዱን ማህበረሰብ ተሳትፎ እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በተለይም ከለውጡ በኋላ በተደረጉ የፖሊሲና የአስተዳደር እርምጃዎች የግሉ ዘርፍ መነቃቃት አሳይቷል ብለዋል።
በመካከለኛና አነስተኛ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑንም ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026