የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ባለፉት ስድስት ወራት ሶስት ሺህ መብቶች ተመዝግበዋል - ባለስልጣኑ

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን በ2017 በጀት አመት ስድስት ወራት ሶስት ሺህ መብቶችን መመዝገቡን ገልጿል።

ባለሥልጣኑ ለቅጅና ተዛማጅ መብቶች፣ ለፓተንቶች(የግልጋሎት ሞዴሎችን ጨምሮ)፣ ለኢንዱስትሪያዊ ንድፎች እና ለንግድ ምልክቶች የመብት ጥብቃ ያደርጋል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ባለስልጣኑ በርካታ አመታት ማስቆጠሩን ተናግረዋል።

በእነዚህ አመታት በርካታ ስራዎች ቢያከናውንም በሚፈለገው ልክ እንዳልነበርም ጨምረው ገልፀዋል።

ለአብነትም እስከ 2015 ድረስ በዓመት በሁሉም መብቶች ጥቂት ምዝገባ ማከናወኑን ጠቅሰዋል።

ተቋሙ ባለፉት 20 አመታት 500 ፓተንት መመዝገቡን ተናግረው፤ ይህን ለማሻሻል የምዝገባ ስርዓቱ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ገልፀዋል።

በዚህም በ2017 በጀት አመት ስድስት ወራት ሶስት ሺህ መብቶች መመዝገቡን ተናግረው፤ የቅጅና ተዛማጅ፣ ፓተንት እና የንግድ ምልክት መብቶችን መመዝገቡን ነው የተናገሩት።

አሁን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎች አበረታች ቢሆኑም በሚፈለገው ደረጃ ላይ አለመድረሱንም ይገልጻሉ።

ይህም የሆነበት ምክንያት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከናወኑ የምርምር ውጤቶችን ከማሳተም ባሻገር ፓተንት እንዲወጣባቸው ስለማይደረግ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዚህም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚያከናውኗቸውን የምርምር ስራዎች ከማሳተም ባሻገር ወደ ፓተንት እንዲያሻግሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.