
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን በ2017 በጀት አመት ስድስት ወራት ሶስት ሺህ መብቶችን መመዝገቡን ገልጿል።
ባለሥልጣኑ ለቅጅና ተዛማጅ መብቶች፣ ለፓተንቶች(የግልጋሎት ሞዴሎችን ጨምሮ)፣ ለኢንዱስትሪያዊ ንድፎች እና ለንግድ ምልክቶች የመብት ጥብቃ ያደርጋል።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ባለስልጣኑ በርካታ አመታት ማስቆጠሩን ተናግረዋል።
በእነዚህ አመታት በርካታ ስራዎች ቢያከናውንም በሚፈለገው ልክ እንዳልነበርም ጨምረው ገልፀዋል።
ለአብነትም እስከ 2015 ድረስ በዓመት በሁሉም መብቶች ጥቂት ምዝገባ ማከናወኑን ጠቅሰዋል።
ተቋሙ ባለፉት 20 አመታት 500 ፓተንት መመዝገቡን ተናግረው፤ ይህን ለማሻሻል የምዝገባ ስርዓቱ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ገልፀዋል።
በዚህም በ2017 በጀት አመት ስድስት ወራት ሶስት ሺህ መብቶች መመዝገቡን ተናግረው፤ የቅጅና ተዛማጅ፣ ፓተንት እና የንግድ ምልክት መብቶችን መመዝገቡን ነው የተናገሩት።
አሁን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎች አበረታች ቢሆኑም በሚፈለገው ደረጃ ላይ አለመድረሱንም ይገልጻሉ።
ይህም የሆነበት ምክንያት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከናወኑ የምርምር ውጤቶችን ከማሳተም ባሻገር ፓተንት እንዲወጣባቸው ስለማይደረግ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚያከናውኗቸውን የምርምር ስራዎች ከማሳተም ባሻገር ወደ ፓተንት እንዲያሻግሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026