
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ):- ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም ከሁለት ቀን በኋላ በአዲስ አበባ ይደረጋል።
ፎረሙ “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና ዕድሎች” በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት አካል በሆነው የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል የተዘጋጀ ነው።
ከመጋቢት 10 እስከ 12 በሚካሄደው ፎረም የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ።
አፍሪካ የዓለምን 30 በመቶ የማዕድን ክምችት የያዘች ሲሆን የማዕድን ሀብቱ ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለኢንዱስትሪ መስፋፋትና የአረንጓዴ ኃይል ሽግግር ጠንካራ መሰረት መሆኑን ህብረቱ አመልክቷል።
ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ያሉ መዋቅራዊ ዕክሎች መፍታትና እድሎች መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል።
በፎረሙ የማዕድን ቁፋሮን ስርዓትን ማዘመን፣ የካርቦን ልህቀትን መቀነስና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ውይይት ይደረጋል።
በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር አጣጥሞ በማስኬድ ጠንካራ አጋርነት መፍጠር ሌላኛው የፎረሙ አጀንዳ ነው።
ማዕከሉ የአፍሪካ የማዕድን ሀብቶች ለአህጉሪቷ ዘላቂ ልማትና ሁሉን አቀፍ እድገት ያላቸው አበርክቶ ማሳደግ ላይ እንደሚሰራ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም እ.አ.አ በ2022 በሩዋንዳ ኪጋሊ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026