የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ሶስተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም በኢትዮጵያ ይካሄዳል

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ):- ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም ከሁለት ቀን በኋላ በአዲስ አበባ ይደረጋል።

ፎረሙ “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና ዕድሎች” በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት አካል በሆነው የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል የተዘጋጀ ነው።

ከመጋቢት 10 እስከ 12 በሚካሄደው ፎረም የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ።

አፍሪካ የዓለምን 30 በመቶ የማዕድን ክምችት የያዘች ሲሆን የማዕድን ሀብቱ ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለኢንዱስትሪ መስፋፋትና የአረንጓዴ ኃይል ሽግግር ጠንካራ መሰረት መሆኑን ህብረቱ አመልክቷል።

ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ያሉ መዋቅራዊ ዕክሎች መፍታትና እድሎች መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል።

በፎረሙ የማዕድን ቁፋሮን ስርዓትን ማዘመን፣ የካርቦን ልህቀትን መቀነስና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ውይይት ይደረጋል።

በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር አጣጥሞ በማስኬድ ጠንካራ አጋርነት መፍጠር ሌላኛው የፎረሙ አጀንዳ ነው።

ማዕከሉ የአፍሪካ የማዕድን ሀብቶች ለአህጉሪቷ ዘላቂ ልማትና ሁሉን አቀፍ እድገት ያላቸው አበርክቶ ማሳደግ ላይ እንደሚሰራ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።

ሁለተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም እ.አ.አ በ2022 በሩዋንዳ ኪጋሊ መካሄዱ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.