
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ):- ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም ከሁለት ቀን በኋላ በአዲስ አበባ ይደረጋል።
ፎረሙ “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና ዕድሎች” በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት አካል በሆነው የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል የተዘጋጀ ነው።
ከመጋቢት 10 እስከ 12 በሚካሄደው ፎረም የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ።
አፍሪካ የዓለምን 30 በመቶ የማዕድን ክምችት የያዘች ሲሆን የማዕድን ሀብቱ ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለኢንዱስትሪ መስፋፋትና የአረንጓዴ ኃይል ሽግግር ጠንካራ መሰረት መሆኑን ህብረቱ አመልክቷል።
ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ያሉ መዋቅራዊ ዕክሎች መፍታትና እድሎች መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል።
በፎረሙ የማዕድን ቁፋሮን ስርዓትን ማዘመን፣ የካርቦን ልህቀትን መቀነስና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ውይይት ይደረጋል።
በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር አጣጥሞ በማስኬድ ጠንካራ አጋርነት መፍጠር ሌላኛው የፎረሙ አጀንዳ ነው።
ማዕከሉ የአፍሪካ የማዕድን ሀብቶች ለአህጉሪቷ ዘላቂ ልማትና ሁሉን አቀፍ እድገት ያላቸው አበርክቶ ማሳደግ ላይ እንደሚሰራ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም እ.አ.አ በ2022 በሩዋንዳ ኪጋሊ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026