
ባህርዳር፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፦በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በግንባታ ላይ የነበሩ 14 ኢንዱስትሪዎች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በመታገዝ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የኢንዱስትሪ ልማት ቡድን መሪ አቶ አቤል ኢሳኢያስ ለኢዜአ እንደገለፁት ወደ ማምረት የተሸጋገሩት ኢንዱስትሪዎች ከ592 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ናቸው።
ኢንዱስትሪዎቹ በኬሚካል፣ በሳሙና፣ በበቆሎ ስታርች፣ በፓስታ፣ በጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ በእብነበረድ፣ በብረታ ብረትና በመኪና ፊልትሮ ማምረት ስራ ላይ የተሰማሩ ናቸው ብለዋል።
ባለድርሻ ተቋማትም በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በመመራት የመብራት፣ የውሃ፣ የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በማሟላታቸው ኢንዱስትሪዎቹ ፈጥነው ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ ማስቻሉን ገልጸዋል።
ኢንዱስትሪዎቹ ለ747 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ጠቁመው ግንባታቸውን ያጠናቀቁ 10 ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍም ወደ ማምረት ለማሸጋገር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የዩኒክ ፓስታና ማካሮኒ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ጌቱ ያዩ፤ በተደረገላቸው ድጋፍ ፋብሪካውን ወደ ማምረት ስራ እንዲገባ ማድረጋቸውን ገልፀዋል።
አሁን ላይ ፋብሪካው በቀን እስከ 150 ኩንታል ፓስታ እያመረተ ለገበያ እያቀረበ መሆኑን ገልፀው በሙሉ አቅሙ ወደ ማምረት ሲሸጋገር ወደ 400 ኩንታል የማሳደግ አቅም እንዳለውም ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የመብራት፣ የውሃና የመንገድ መሰረተ ልማት እንዲሟላ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው ለ122 ሰራተኞችም ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን አውስተዋል።
በከተማ አስተዳደሩ እስካሁን 342 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በማምረት ስራ ላይ እንደሚገኙም ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026