የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ሶስተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም ዛሬ ይጀመራል

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል።

ፎረሙ የሚካሄደው “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና እድሎች” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

የአፍሪካ ህብረት ልዩ ኤጀንሲ የሆነው የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል ፎረሙን አዘጋጅቷል።

ፎረሙ በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ላይ የሚታዩ መዋቅራዊ እክሎችን መፍታት እና እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክር ከአፍሪካ ህብረት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ባህላዊ የማዕድን ማውጣት ዘዴን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መተካት፣ ወደ ከባቢ አየር የሚገባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማምጣት የሚያስችሉ መንገዶች ላይም ውይይት እንደሚደረግ አመልክቷል።

በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር አጣጥሞ በማስኬድ ጠንካራ አጋርነት መፍጠር ሌላኛው የፎረሙ አጀንዳ ነው።

የማዕድን ሀብት ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ትኩረት የሚሹ የህብረተስብ ክፍሎችን አቅም መገንባት እና ድምጻቸው እንዲሰማ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል።

በፎረሙ ላይ የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ።

ፎረሙ እስከ መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.