አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል።
ፎረሙ የሚካሄደው “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና እድሎች” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
የአፍሪካ ህብረት ልዩ ኤጀንሲ የሆነው የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል ፎረሙን አዘጋጅቷል።
ፎረሙ በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ላይ የሚታዩ መዋቅራዊ እክሎችን መፍታት እና እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክር ከአፍሪካ ህብረት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ባህላዊ የማዕድን ማውጣት ዘዴን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መተካት፣ ወደ ከባቢ አየር የሚገባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማምጣት የሚያስችሉ መንገዶች ላይም ውይይት እንደሚደረግ አመልክቷል።
በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር አጣጥሞ በማስኬድ ጠንካራ አጋርነት መፍጠር ሌላኛው የፎረሙ አጀንዳ ነው።
የማዕድን ሀብት ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ትኩረት የሚሹ የህብረተስብ ክፍሎችን አቅም መገንባት እና ድምጻቸው እንዲሰማ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል።
በፎረሙ ላይ የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ።
ፎረሙ እስከ መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025