የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ ለጋምቢያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ልምድ አካፈለች

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ፦ ኢትዮጵያ ከጋምቢያ ለመጣ ልዑክ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ልምድ አካፈለች።

በጋምቢያ የማዕከላዊ ባንክ ተቀዳሚ ምክትል ገዥ አብዱላዮ ሲረህ ጃሎ(ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በመገኘት ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢነርጂ ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ጋር ተወያይቷል፡፡

ውይይቱም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተሞክሮ ላይ ትኩረት የደረገ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ሀይል ከውሃ የማመንጨት የዳበረ ተሞክሮ እንዳላት አንስተው፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአፍሪካ በትልቅነቱም ሆነ፤ በፋይናንስ ምንጭና ከህዝባዊ ተሳትፎ አንጻር በርካታ ተሞክሮዎች የተገኘበት ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

የህዳሴ ግድብ በመንግስት ቁርጠኝነትና በህዝቦች የነቃ ተሳትፎ በራስ የፋይናንስ አቅም የተገነባና የህዝቦችን አንድነት ያጠናከረ ታላቅ ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንበታ እንዳይሳካ የተደረጉ ጥረቶችን በሙሉ በጥበብ በማለፍ ግድቡ ሀይል ማመንጨት ጀምሯል ብለዋል፡፡

ከታላቁ ህዳሴ ግድብ የድርድር ሂደቶች ጋር ተያይዞ ባደረጉት ገለጻ የአፍሪካን ጉዳዮች በአፍሪካውያን በሚል መርህ የድርድር ሂደቶች የተመሩበት አግባብ ትልቅ ማስተማሪያ ሆኗል በማለት ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.