
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ፦ ኢትዮጵያ ከጋምቢያ ለመጣ ልዑክ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ልምድ አካፈለች።
በጋምቢያ የማዕከላዊ ባንክ ተቀዳሚ ምክትል ገዥ አብዱላዮ ሲረህ ጃሎ(ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በመገኘት ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢነርጂ ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) ጋር ተወያይቷል፡፡
ውይይቱም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተሞክሮ ላይ ትኩረት የደረገ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ሀይል ከውሃ የማመንጨት የዳበረ ተሞክሮ እንዳላት አንስተው፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአፍሪካ በትልቅነቱም ሆነ፤ በፋይናንስ ምንጭና ከህዝባዊ ተሳትፎ አንጻር በርካታ ተሞክሮዎች የተገኘበት ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የህዳሴ ግድብ በመንግስት ቁርጠኝነትና በህዝቦች የነቃ ተሳትፎ በራስ የፋይናንስ አቅም የተገነባና የህዝቦችን አንድነት ያጠናከረ ታላቅ ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንበታ እንዳይሳካ የተደረጉ ጥረቶችን በሙሉ በጥበብ በማለፍ ግድቡ ሀይል ማመንጨት ጀምሯል ብለዋል፡፡
ከታላቁ ህዳሴ ግድብ የድርድር ሂደቶች ጋር ተያይዞ ባደረጉት ገለጻ የአፍሪካን ጉዳዮች በአፍሪካውያን በሚል መርህ የድርድር ሂደቶች የተመሩበት አግባብ ትልቅ ማስተማሪያ ሆኗል በማለት ገልጸዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026