የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በአፍሪካ ትልቁን አየር መንገድ ለመገንባት በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክቶች ትኩረት በመስጠት በአፍሪካ ትልቁን አየር መንገድ ለመገንባት በርካታ ሥራዎች እያከናወነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።

በማብራሪያቸውም፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፕላን ቁጥር፣ በመዳረሻ ብዛት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡

ከዚህም ባለፈ አየር መንገዶችን አስመርቆ ሥራ በማስጀመር እና የበረራ ድግግሞሽን በማሳደግ አገልግሎቱንና ትርፋማነቱን ጨምሯል ብለዋል፡፡

የዲዛይንና የፋይናንስ ጉዳዮች ሲጠናቀቁ ሥራው እንደሚጀመር ገልጸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፋይናንስ አቅሙ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ የማይተናነስ ሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ተጨማሪ መርከቦችን በማስገባት ሥራውን ለማዘመንና ትርፋማነቱን ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የባቡር ትራንስፖርት አፈፃፀም ከአምናው ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ መጨመሩንና የዲጂታል ግብይት ከእጥፍ በላይ ማደጉን ተናግረዋል፡፡

በቅርቡ የተጀመረው የካፒታል ገበያ ለአምስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ፈቃድ መስጠቱን አንስተው፤ የዲጂታል ግብይቱና የንግድ ስርዓቱ በዚያው ልክ እየዘመነ የሚሄድበትን እድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.