
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክቶች ትኩረት በመስጠት በአፍሪካ ትልቁን አየር መንገድ ለመገንባት በርካታ ሥራዎች እያከናወነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
በማብራሪያቸውም፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፕላን ቁጥር፣ በመዳረሻ ብዛት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
ከዚህም ባለፈ አየር መንገዶችን አስመርቆ ሥራ በማስጀመር እና የበረራ ድግግሞሽን በማሳደግ አገልግሎቱንና ትርፋማነቱን ጨምሯል ብለዋል፡፡
የዲዛይንና የፋይናንስ ጉዳዮች ሲጠናቀቁ ሥራው እንደሚጀመር ገልጸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፋይናንስ አቅሙ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ የማይተናነስ ሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ተጨማሪ መርከቦችን በማስገባት ሥራውን ለማዘመንና ትርፋማነቱን ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
የባቡር ትራንስፖርት አፈፃፀም ከአምናው ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ መጨመሩንና የዲጂታል ግብይት ከእጥፍ በላይ ማደጉን ተናግረዋል፡፡
በቅርቡ የተጀመረው የካፒታል ገበያ ለአምስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ፈቃድ መስጠቱን አንስተው፤ የዲጂታል ግብይቱና የንግድ ስርዓቱ በዚያው ልክ እየዘመነ የሚሄድበትን እድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026