
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክቶች ትኩረት በመስጠት በአፍሪካ ትልቁን አየር መንገድ ለመገንባት በርካታ ሥራዎች እያከናወነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
በማብራሪያቸውም፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፕላን ቁጥር፣ በመዳረሻ ብዛት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
ከዚህም ባለፈ አየር መንገዶችን አስመርቆ ሥራ በማስጀመር እና የበረራ ድግግሞሽን በማሳደግ አገልግሎቱንና ትርፋማነቱን ጨምሯል ብለዋል፡፡
የዲዛይንና የፋይናንስ ጉዳዮች ሲጠናቀቁ ሥራው እንደሚጀመር ገልጸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፋይናንስ አቅሙ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ የማይተናነስ ሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ተጨማሪ መርከቦችን በማስገባት ሥራውን ለማዘመንና ትርፋማነቱን ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
የባቡር ትራንስፖርት አፈፃፀም ከአምናው ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ መጨመሩንና የዲጂታል ግብይት ከእጥፍ በላይ ማደጉን ተናግረዋል፡፡
በቅርቡ የተጀመረው የካፒታል ገበያ ለአምስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ፈቃድ መስጠቱን አንስተው፤ የዲጂታል ግብይቱና የንግድ ስርዓቱ በዚያው ልክ እየዘመነ የሚሄድበትን እድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026