የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ወጣቱ በሳል የሆነ የማኀበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን መከተል ይገባዋል - ወጣቶች

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፡- ወጣቱ በሳል የሆነ የማኀበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በመከተል እንደሚገባው ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገለጹ።

ማህበራዊ ሚዲያ የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዲሁም አኗኗር ቀላል እያደረገው መጥቷል።

በአዲስ አበባ ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚወጡ መረጃዎችን በሙሉ ከመውሰድ ይልቅ አጣርቶ መጠቀም ይገባል ይላሉ።

ወጣት ህይወት አምባው እንዳለችው፤ አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የተለያየ ዓላማን በመያዝ ሀሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ይስተዋላል።

በመሆኑም መረጃዎቹን ከመጠቀም በፊት ትክክለኛነታቸውን ማጣራት ይገባል ብላለች።

ወጣት ህይወት በማህበራዊ ሚዲያ የሚለቀቁ መረጃዎች ምንጫቸው ከየት ነው? ትክክለኛነቱስ ምን ያህል ነው? የሚለውን ማጤን ይገባልም ስትል ትመክራለች።

ወጣቶች ትክክለኛ መረጃዎችን ከትክክለኛ ምንጮች በመውሰድ ራሳችንን ከሀሰተኛ መረጃ ከመጠበቅ ባለፈ ለህዝቦች አብሮነት መስራት አለብን ብላለች።

ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለምን ዓላማ ነው የምንጠቀመው የሚለውን ቆም ብለን ልናስብ ይገባል ያለው ደግሞ ወጣት ሃይለማሪያም ተሰማ ነው።

የወጣቱ ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ብስለት የተሞላበት ሊሆን እንደሚገባና ሚዲያውን ለበጎ ነገር መጠቀም ይገባል ብሏል።

በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ተከታዮችን ማፍራት መቻሉን የጠቀሰው ወጣት በረከት ከበደ በበኩሉ በማህበራዊ ሚዲያው የሚያስተላልፈውን መልዕክት ለሀገርና ለሕዝብ ምን ያህል ይጠቅማል የሚለውን የመመዘን ልምድ እንዳለው ገልጿል።

በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያለውን ልምድ ለወጣቶች በማካፈል የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑንም ነው የጠቆመው።

ወጣት መንበረ መልኬ በበኩሉ ወጣቱ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለሀገር የሚጠቅም ገንቢ ሚና እንዲጫወት ግንዛቤን የማስፋት ሥራ ሊጠናከር ይገባል ብሏል።

ለዚህም ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን መስጠት ላይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ በመጠቆም።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.