
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017(ኢዜአ)፡- ወጣቱ በሳል የሆነ የማኀበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በመከተል እንደሚገባው ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ገለጹ።
ማህበራዊ ሚዲያ የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዲሁም አኗኗር ቀላል እያደረገው መጥቷል።
በአዲስ አበባ ኢዜአ ያነጋገራቸው ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚወጡ መረጃዎችን በሙሉ ከመውሰድ ይልቅ አጣርቶ መጠቀም ይገባል ይላሉ።
ወጣት ህይወት አምባው እንዳለችው፤ አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የተለያየ ዓላማን በመያዝ ሀሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ይስተዋላል።
በመሆኑም መረጃዎቹን ከመጠቀም በፊት ትክክለኛነታቸውን ማጣራት ይገባል ብላለች።
ወጣት ህይወት በማህበራዊ ሚዲያ የሚለቀቁ መረጃዎች ምንጫቸው ከየት ነው? ትክክለኛነቱስ ምን ያህል ነው? የሚለውን ማጤን ይገባልም ስትል ትመክራለች።
ወጣቶች ትክክለኛ መረጃዎችን ከትክክለኛ ምንጮች በመውሰድ ራሳችንን ከሀሰተኛ መረጃ ከመጠበቅ ባለፈ ለህዝቦች አብሮነት መስራት አለብን ብላለች።
ወጣቶች ማህበራዊ ሚዲያን ለምን ዓላማ ነው የምንጠቀመው የሚለውን ቆም ብለን ልናስብ ይገባል ያለው ደግሞ ወጣት ሃይለማሪያም ተሰማ ነው።
የወጣቱ ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ብስለት የተሞላበት ሊሆን እንደሚገባና ሚዲያውን ለበጎ ነገር መጠቀም ይገባል ብሏል።
በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ተከታዮችን ማፍራት መቻሉን የጠቀሰው ወጣት በረከት ከበደ በበኩሉ በማህበራዊ ሚዲያው የሚያስተላልፈውን መልዕክት ለሀገርና ለሕዝብ ምን ያህል ይጠቅማል የሚለውን የመመዘን ልምድ እንዳለው ገልጿል።
በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያለውን ልምድ ለወጣቶች በማካፈል የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑንም ነው የጠቆመው።
ወጣት መንበረ መልኬ በበኩሉ ወጣቱ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለሀገር የሚጠቅም ገንቢ ሚና እንዲጫወት ግንዛቤን የማስፋት ሥራ ሊጠናከር ይገባል ብሏል።
ለዚህም ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን መስጠት ላይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ በመጠቆም።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026