
ባህርዳር ፤መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በዲጅታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ።
በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ከዳኞችና ተገልጋዮች ጋር በዛሬው እለት ውይይት አካሂዷል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ እፀገነት መንግስቱ፤ በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ እየተሰጠ ያለው የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ የሚበረታታ መሆኑን አንስተው በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
የፍትህ ዘርፉን ፈጣን፣ ግልጽ፣ ተአማኒና ሚዛናዊነቱ የተጠበቀ እንዲሆን በሚደረገው ጥረት የድጂታል አሰራሮችን ማስፋትና ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህ ረገድ በአማራ ክልል የተጀመሩ ጥረቶችና እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ጉብኝትም የሀገሪቱን የፍትህ ትራንስፎርሜሽን መርሃ-ግብር አተገባበር ለመገምገም መሆኑን ገልጸዋል።
የዳኝነት አካላት የለውጥ ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም ለመመልከትና አፈጻጸሙን ከተገልጋዩ በመረዳት ግብረመልሶችን በመቀበል ለቀጣይ ስራ አቅጣጫ ለማመላከት መሆኑንም አስረድተዋል።
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህንጻ የእድሳት ሂደት በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውን ጠቁመው ይህም ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026