ባህርዳር ፤መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በዲጅታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ።
በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ከዳኞችና ተገልጋዮች ጋር በዛሬው እለት ውይይት አካሂዷል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ እፀገነት መንግስቱ፤ በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ እየተሰጠ ያለው የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ የሚበረታታ መሆኑን አንስተው በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
የፍትህ ዘርፉን ፈጣን፣ ግልጽ፣ ተአማኒና ሚዛናዊነቱ የተጠበቀ እንዲሆን በሚደረገው ጥረት የድጂታል አሰራሮችን ማስፋትና ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህ ረገድ በአማራ ክልል የተጀመሩ ጥረቶችና እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ጉብኝትም የሀገሪቱን የፍትህ ትራንስፎርሜሽን መርሃ-ግብር አተገባበር ለመገምገም መሆኑን ገልጸዋል።
የዳኝነት አካላት የለውጥ ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም ለመመልከትና አፈጻጸሙን ከተገልጋዩ በመረዳት ግብረመልሶችን በመቀበል ለቀጣይ ስራ አቅጣጫ ለማመላከት መሆኑንም አስረድተዋል።
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህንጻ የእድሳት ሂደት በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውን ጠቁመው ይህም ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025