
ባህርዳር ፤መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በዲጅታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ።
በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ከዳኞችና ተገልጋዮች ጋር በዛሬው እለት ውይይት አካሂዷል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ እፀገነት መንግስቱ፤ በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ እየተሰጠ ያለው የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ የሚበረታታ መሆኑን አንስተው በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
የፍትህ ዘርፉን ፈጣን፣ ግልጽ፣ ተአማኒና ሚዛናዊነቱ የተጠበቀ እንዲሆን በሚደረገው ጥረት የድጂታል አሰራሮችን ማስፋትና ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህ ረገድ በአማራ ክልል የተጀመሩ ጥረቶችና እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ጉብኝትም የሀገሪቱን የፍትህ ትራንስፎርሜሽን መርሃ-ግብር አተገባበር ለመገምገም መሆኑን ገልጸዋል።
የዳኝነት አካላት የለውጥ ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም ለመመልከትና አፈጻጸሙን ከተገልጋዩ በመረዳት ግብረመልሶችን በመቀበል ለቀጣይ ስራ አቅጣጫ ለማመላከት መሆኑንም አስረድተዋል።
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህንጻ የእድሳት ሂደት በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውን ጠቁመው ይህም ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026