መቀሌ፤ መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- የመቀሌ ከተማን ውብና ፅዱ ለማድረግ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከ4 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የመቀሌ ከተማ ማኑፋክቸሪንግ፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች ለኢዜአ እንዳሉት በሚቀጥሉት ሶስት ወራት ከተማውን ፅዱና ውብ ለማድረግ ከ588 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቧል።
የመቀሌ ከተማ የማኑፋክችሪንግ፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሮ ልዕልቲ ፍስሃ፤ በተያዘው በጀት ዓመት ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ባሉት ሶስት ወራት 161 ኪሎ ሜትር መንገድ ጠጠር የማልበስ እና 3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ ደግሞ በኮብል ስቶን የማስዋብ ስራ እንደሚሰራም ገልፀዋል።
በኮብል ስቶን የማስዋብ ስራውና በሌሎች የልማት ተግባራትም በመቀሌ ከተማ የሚገኙ ሰባት ክፍለ ከተሞችን ውብና ፅዱ እንዲሆኑ እንደሚሰራ ገልፀው ወደ ተግባር ለመግባት ሲደረግ የቆየው ዝግጅት ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁን ተናግረዋል።
በ161 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ የማልበስ ሥራውም 15 የገጠር ቀበሌዎችን ከመቀሌ ጋር በማገናኘት ነዋሪዎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።
በዚህ ስራም ለ4ሺህ 490 ሰዎች የስራ እድል እንደሚፈጠር ገልፀው ከተጠቀሱት ውስጥ 2ሺህ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ተግባሩን ለመከወን የተመለመሉና በ23 ማህበራት የተደራጁ ወጣቶች ስራውን በብቃትና በፍጥነት ለማከናወን የሚያስችላቸውን በተግባር የተደገፈ የሙያ ስልጠና መሰጠቱን የገለጹት ደግሞ የመቀሌ የኢንተርፕራይዝ ጥናትና ማቋቋም ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አለምሰገድ ገብረህይወት ናቸው።
በኮብል ስቶን ማስዋብ ስራና ሌሎች የልማት ስራዎች ላይ ለመሰማራት የተደራጁት ወጣቶች የአካባቢያቸውን ልማት ከማፋጠን ባለፈ ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያሸጋግራቸውን ገቢ ለማግኘት እንደሚያስችላቸውም ገልፀዋል።
በከተማው የሀድነት ክፍለ ከተማ ነዋሪዋ ወጣት መአርግ ሃይሉ በልማት ስራው ተሳትፋ ተጠቃሚ ለመሆን ተስፋ ማድረጓን ተናግራለች።
በከተማው የሃውልት ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወጣት አብራሃም መብራህቱ በበኩሉ፣ ወጣቶች የተፈጠረውን ሰላም በመጠበቅ በልማት ራሳችንን ለመለወጥ መትጋት አለብን ብሏል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025