የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ባንኩ በስምንት ወራቱ ከ264 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ለደንበኞች አቅርቧል- አቶ አቤ ሳኖ

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ስምንት ወራት ከ264 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ለደንበኞች ማቅረቡን የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገለጹ።

717 ሺህ ደንበኞች በዲጂታል አማራጭ የብድር ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የተቋሙን የስምንት ወራት አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ተወካዮች ምክር የመንግስት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቅርበዋል።

ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ባንኩ ብድርን ከማስፋፋት እና የዜጎችን የፋይናንስ ተጠቃሚነት ከማሳደግ አንፃር አዳዲስ የብድር አይነቶችን እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡

በዚህም ባንኩ ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ 264 ነጥብ 65 ቢሊዮን ብር ብድር ለደንበኞቹ ማቅረቡን ገልጸው ከዚህ ውስጥ 88 ነጥብ 2 በመቶው የተሰጠው ለግሉ ዘርፍ እንደሆነ አመልክተዋል።

ጠቅላላ የተሰጠ የብድር መጠን ብር 1 ነጥብ 39 ትሪሊዮን በር መድረሱንም ጠቁመዋል።

የብድር ተደራሽነትን ከማስፋት አንፃር ባንኩ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር በዲጂታል አማራጭ ብድሮችን እያቀረበ መሆኑን ነው ያስረዱት።

ፕሬዝዳንቱ በዲጂታል አማራጭ ባለፉት ስምንት ወራት አጠቃላይ ብር 3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብድር ማቅረብ መቻሉንና በፈረንጆች እስከ ፌብሩዋሪ 28 ቀን 2025 ድረስ 717 ሺህ ደንበኞች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ባንኩ የዜጎችን የስራ ተነሳሽነት ከመደገፍ አንጻር ጥሩ የመስራት አቅም ላላቸው ስራ ፈጣሪዎች የብድር አገልግሎት ለመስጠት አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉንም ጠቁመዋል።

በዲጂታል አማራጭ የብድር አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው በሙከራ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ፕሬዚዳንቱ መግለጻቸውን ከባንኩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.