አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ዛሬ በጣልያን ሮም በተጀመረው 177ኛው የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) የካውንስል ስብሰባ እየተሳተፈች ነው።
በጣልያን የኢትዮጵያ አምባሳደር እና በዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት፣ በዓለም የምግብ ፕሮግራም እና የዓለም አቀፉ የግብርና ልማት ፈንድ የኢትዮጵያ ቋሚ ተጠሪ አምባሳደር ደሚቱ ሃምቢሳ በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል።
አምባሳደር ደሚቱ ሀገራት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እያከናወኑ ያሉትን ውጤታማ ስራና በዚሁ ረገድ እያጋጠማቸው ያለውን ፈተና አስመልክተው አፍሪካን ወክለው ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
በስብሰባው ፋኦ በስትራቴጂክ እቅዱ ላይ በመወያየት አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ሀገራት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እያጋጠማቸው ያለው ፈተና እና መፍትሄዎቻቸው እንዲሁም ድንገተኛ አደጋ በሚያጋጥማቸው ወቅት አፋጣኝ ምላሽ መስጠት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራል።
ስብሰባው እስከ ሚያዚያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025