
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውበት ያሳየና የቱሪዝም መስህብነቷን ያሳደገ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ግለሰቦች ገለጹ፡፡
የኮሪደር ልማት ስራዎችን በባለቤትነት መጠበቅና መንከባከብ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በአዲስ አበባ የተገነቡ እና እየተገነቡ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች ከተማዋን እንደ ስሟ ውብና ሳቢ በማድረግ ተመራጭነቷን ያሳደገ ነው፡፡

የከተማዋ የኮሪደር ልማት የነዋሪዎችን የአኗኗር ዘይቤ ያሻሻለ፣ ከተማዋን የሚመጥን፣ ዘመኑን የዋጀ የመሰረተ ልማት አቅርቦት የጨመረና የከተማዋን ገጽታ የቀየረ ፕሮጀክት ነው፡፡
ኢዜአ ያነጋገራቸው የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን የዕድገት ደረጃ ይበልጥ የሚያሣልጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል መንሱር ጀማል እንተገለጸው በሀገር ደረጃ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ዜጎች ምቹና ዘመናዊ የሆነ ከባቢ እንዲኖራቸው ያስቻለ፤ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ያሳደገ ነው፡፡
በመዲናዋ የተከናወኑና እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችም አዲስ አበባ እንደስሟ ውብ፣ ጽዱና ደረጃዋን የጠበቀች እንድትሆን ማስቻሉን ገልጿል፡፡
መንግስት የዜጎችን የልማት ጥያቄ ለመመለስና የሀገርን ገጽታ ለመገንባት የሚያከናውናቸው ተግባራት ከግብ እንዲደርሱ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብሏል፡፡

አርቲስት ሙሉነህ ዘለቀ በበኩሉ በሀገር ደረጃ እየተተገበሩ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች የቱሪስት መዳረሻነትን ያሳደጉ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡
በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች ላይ የተገነቡ የህጻናት መጫወቻዎች፣ የመዝናኛ እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ጨምሮ ሌሎች ልማቶች መጪውን ትውልድ የሚመጥኑ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን የመለሱ መሆናቸውን ገልጿል፡፡
የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በባለቤትነት መጠበቅና መንከባከብ እንደሚገባም ጠቁሟል፡፡

የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ለረጅም ዓመታት አገልግሎት እንዲሰጡ ሁሉም አካል መጠበቅና መንከባከብ እንደሚገባው የገለጸው ደግሞ አርቲስት ኤልያስ ተባባል ነው፡፡
የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ሌሎችም ከተሞች ልምድ እየቀሰሙበት የሚገኝ መልካም ተሞክሮ ነው።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026