የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት አሠጣጥን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር)

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2 /2017(ኢዜአ)፦ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የአገልግሎት አሠጣጥን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡


የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቋጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀምሯል።


የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ እንደገለጹት፥ በትራንስፖርት ዘርፍ የሚሰጠውን የአገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተሰርተዋል፡፡


ዛሬ የተመረቀው ሲስተም የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎትን በማዘመን እና በማቀላጠፍ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ገልጸዋል፡፡


በዘርፉ የሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጦችን ዲጂታል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ ሌሎች በዘርፉ ተግባራዊ የሚደረጉ ቴክኖሎጂዎችም በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገቡ ጠቁመዋል፡፡


የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያዘምነው ሲስተም በተባለው ጊዜ መጠናቀቁን አስታውቀዋል።


ኢንስቲትዩቱ የአገልግሎት አሰጣጦችን የሚያቀላጥፉና ችግሮችን የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን የማልማቱን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አቅም የመገንባት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።


የተመረቀው ሲስተም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያበለጸገው መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.