
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2 /2017(ኢዜአ)፦ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የአገልግሎት አሠጣጥን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቋጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀምሯል።
የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ እንደገለጹት፥ በትራንስፖርት ዘርፍ የሚሰጠውን የአገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተሰርተዋል፡፡
ዛሬ የተመረቀው ሲስተም የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎትን በማዘመን እና በማቀላጠፍ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ገልጸዋል፡፡
በዘርፉ የሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጦችን ዲጂታል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ ሌሎች በዘርፉ ተግባራዊ የሚደረጉ ቴክኖሎጂዎችም በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገቡ ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያዘምነው ሲስተም በተባለው ጊዜ መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
ኢንስቲትዩቱ የአገልግሎት አሰጣጦችን የሚያቀላጥፉና ችግሮችን የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን የማልማቱን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አቅም የመገንባት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የተመረቀው ሲስተም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያበለጸገው መሆኑ ተገልጿል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026