የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የወላይታ ሶዶ ከተማ የኮሪደር ልማት የከተማውን ውበት ከማጉላት ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ አስተዋጾ እያደረገ ነው--ነዋሪዎች

Apr 11, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 2/2017 (ኢዜአ)፡-በወላይታ ሶዶ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውበት ከማጉላት ባለፈ በርካታ ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት የኮሪደር ልማቱ ከተማን ውብ፣ ፅዱ እና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል።


የከተማው ነዋሪ ወጣት ዎጋሶ ጌታ የኮሪደር ልማት ከመካሄዱ በፊት በከተማዋ በርካታ ስፍራዎች ላይ ቆሻሻ በዘፈቀደ ስለሚጣል ለመጥፎ ጠረን በመዳረግ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን አዳጋች አድርጎት እንደነበር አስታውሷል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የከተማ አስተዳደሩ የከተማዋን ነዋሪዎች በማስተባበር እያከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታና ውበት ከማጉላት ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑን ተናግሯል።


በከተማው ከ40 ዓመት በላይ እንደኖሩ የገለጹት ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ከበቡሽ ዳኛቸው በበኩላቸው ከዚህ ቀደም የነበሩ የከተማዋ መንገዶች ጠባብ እና በነጻነት ለመንቀሳቀስ ምቹ እንዳልነበሩ አስታውሰዋል።

በከተማው የኮሪደር ልማት በመጀመሩ ይህ ችግር መፈታቱንና የትራፊክ አደጋና መሰል ስጋቶችንም አስወግዶልናል ብለዋል ።


መንገዶቹ ከመስፋታቸው ባለፈ ጽዱና ንጹህ መሆናቸው ለህሊና ዕረፍት የሚሰጥ ነው ያሉት ወይዘሮ ከበቡሽ፣ ህብረተሰቡም በኮሪደር በለማ የእግረኛ መንገድ ላይ በእግር የመጓዝ ባህሉ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።

በቀጣይም የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ እንዲስፋፋ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።

የኮሪደር ልማቱ አረንጓዴ ስፍራና የህዝብ መዝናኛንም እንዲያካትት መደረጉ ነዋሪዎችም ሆነ ወደ ከተማው የሚገቡ እንግዶች ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ እያገዘ ነው ያሉት ደግሞ መምህር ታረቀኝ በቀለ ናቸው።


በልማቱ የእግረኞችና የተሽከርካሪ መንገዶች መለየታቸው የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት በማድረግ በኩል ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም ተናግረዋል

የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ጽህፈት ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አስራት ሉንግሶ በበኩላቸው የከተማዋን ገጽታ የሚቀይሩና ተወዳዳሪና ምቹ የሚያደርጉ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


በከተማው 100 መቶ ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ ከሰባት ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል

የኮሪደር ልማት ኢንሼቲቭ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየርና ከማስዋብ አንጻር ያለውን ፋይዳ ህብረተሰቡ በመረዳቱ ያደረገው ድጋፍና አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም አቶ አስራት ጠቅሰዋል።

ፕሮጀክቱ ከተማዋን ጽዱና ለኑሮ ምቹ ከማድረግ ባለፈ ከ300 ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የገለጹት አቶ አስራት፣ በከተማዋ የኮሪደር ልማቱን በማስፋፋት ከተማን ለማዘመንና ተወዳዳሪ ለማድረግ ጠንክረን እንሠራለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026