
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን አበረታች ስራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ወሀብረቢ አሳሰቡ።
የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዕቅድ አፈፃፀምና ቀጣይ ስራዎች ላይ ዛሬ ውይይት ተካሂዷል።
ማህበሩ የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ አዲስ የማህበሩን ፕሬዝዳንትና 11 የቦርድ አባላትን ምርጫ ማካሄዱ የሚታወስ ነው።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ያስሚን ወሀብረቢ ከጠቅላላ ጉባኤው በኋላ በተከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ከማህበሩ አመራሮችና ከቦርዱ አባላት ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ ማህበሩ ሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ባሳተፈ መልኩ የኢትዮጵያን ነጋዴ ሴቶች ለማብቃትና በንግዱ ዘርፍ በሴት ነጋዴዎች ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል ነው ብለዋል።
ማህበሩ ባለፉት ጥቂት ወራት አበረታች ስራዎች ማከናወኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ በኢትዮጵያ ለሚካሄደው የኮሜሳ የሴት ነጋዴዎች የቢዝነስ ኮንፍረንስና ኤግዚቢሽን የዝግጅት ስራ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
በቀጣይም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተደራሽነትን በማስፋትና ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን በማከናወን የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወይዘሮ በረከት ወርቁ በማህበሩ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026