
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን አበረታች ስራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ወሀብረቢ አሳሰቡ።
የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዕቅድ አፈፃፀምና ቀጣይ ስራዎች ላይ ዛሬ ውይይት ተካሂዷል።
ማህበሩ የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ አዲስ የማህበሩን ፕሬዝዳንትና 11 የቦርድ አባላትን ምርጫ ማካሄዱ የሚታወስ ነው።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ያስሚን ወሀብረቢ ከጠቅላላ ጉባኤው በኋላ በተከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ከማህበሩ አመራሮችና ከቦርዱ አባላት ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ ማህበሩ ሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ባሳተፈ መልኩ የኢትዮጵያን ነጋዴ ሴቶች ለማብቃትና በንግዱ ዘርፍ በሴት ነጋዴዎች ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል ነው ብለዋል።
ማህበሩ ባለፉት ጥቂት ወራት አበረታች ስራዎች ማከናወኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ በኢትዮጵያ ለሚካሄደው የኮሜሳ የሴት ነጋዴዎች የቢዝነስ ኮንፍረንስና ኤግዚቢሽን የዝግጅት ስራ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
በቀጣይም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተደራሽነትን በማስፋትና ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን በማከናወን የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወይዘሮ በረከት ወርቁ በማህበሩ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026