የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ማህበሩ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ መቀጠል አለበት

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን አበረታች ስራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ወሀብረቢ አሳሰቡ።

የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዕቅድ አፈፃፀምና ቀጣይ ስራዎች ላይ ዛሬ ውይይት ተካሂዷል።

ማህበሩ የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ አዲስ የማህበሩን ፕሬዝዳንትና 11 የቦርድ አባላትን ምርጫ ማካሄዱ የሚታወስ ነው።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ያስሚን ወሀብረቢ ከጠቅላላ ጉባኤው በኋላ በተከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ከማህበሩ አመራሮችና ከቦርዱ አባላት ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ ማህበሩ ሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ባሳተፈ መልኩ የኢትዮጵያን ነጋዴ ሴቶች ለማብቃትና በንግዱ ዘርፍ በሴት ነጋዴዎች ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል ነው ብለዋል።

ማህበሩ ባለፉት ጥቂት ወራት አበረታች ስራዎች ማከናወኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ በኢትዮጵያ ለሚካሄደው የኮሜሳ የሴት ነጋዴዎች የቢዝነስ ኮንፍረንስና ኤግዚቢሽን የዝግጅት ስራ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

በቀጣይም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተደራሽነትን በማስፋትና ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን በማከናወን የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወይዘሮ በረከት ወርቁ በማህበሩ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.