የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 የቢዝነስ ፎረም ግንቦት 4 እና 5 በአዲስ አበባ ይካሄዳል

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በመጪው ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።


ፎረሙን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እንደተናገሩት፥ የቢዝነስ ፎረሙ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች የተዘጋጀ ነው።


ለ3ኛ ጊዜ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል።


አዳዲስ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማሳወቅ የፎረሙ ዓላማ ነው ብለዋል።


በፎረሙ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣የፖሊሲ አውጪዎች፣አማካሪዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 የቢዝነስ ፎረም ግንቦት 4 እና 5 በአዲስ አበባ ይካሄዳል


አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በመጪው ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።


ፎረሙን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እንደተናገሩት፥ የቢዝነስ ፎረሙ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች የተዘጋጀ ነው።


ለ3ኛ ጊዜ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል።


አዳዲስ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማሳወቅ የፎረሙ ዓላማ ነው ብለዋል።


በፎረሙ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣የፖሊሲ አውጪዎች፣አማካሪዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.