
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በመጪው ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
ፎረሙን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እንደተናገሩት፥ የቢዝነስ ፎረሙ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች የተዘጋጀ ነው።
ለ3ኛ ጊዜ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል።
አዳዲስ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማሳወቅ የፎረሙ ዓላማ ነው ብለዋል።
በፎረሙ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣የፖሊሲ አውጪዎች፣አማካሪዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 የቢዝነስ ፎረም ግንቦት 4 እና 5 በአዲስ አበባ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በመጪው ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
ፎረሙን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እንደተናገሩት፥ የቢዝነስ ፎረሙ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች የተዘጋጀ ነው።
ለ3ኛ ጊዜ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል።
አዳዲስ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማሳወቅ የፎረሙ ዓላማ ነው ብለዋል።
በፎረሙ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣የፖሊሲ አውጪዎች፣አማካሪዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026