
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካቾች ስኬታማ አፈጻጸም መመዝገቡን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) አስታወቁ።
የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀን አፈጻጸም እና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ ያለፉት ዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።

በመድረኩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚና የዘርፎች አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።
የሁለተኛው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ የዘርፎች ምርታማነትና ተወዳዳሪነት ማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ንግድን ከባቢ ማሳደግ እንዲሁም የመንግስት የመፈጸም አቅምን ማጎልበት ዓላማ አድርጎ ወደ ትግበራ መግባቱን አብራርተዋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በአራቱም ምሶሶዎች የተሻለ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰው፤ ይህም የስምንት ነጥብ አራት በመቶ የኢኮኖሚ እድገት ለማስዝገብ የተያዘው እቅድ እንደሚሳካ ያመላከተ ነው ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ ኢንቨስትመንትና ቁጠባ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት ያላቸው ድርሻ መሻሻሉንም ነው የጠቀሱት።
ኢንቨስትመንት ከሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት አኳያ ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረበት 20 ነጥብ 5 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉን አንስተዋል።
የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብ ላይ የተሻለ አፈጻጻም መመዝገቡን የተናገሩት ሚኒስትሯ፤ የውጭ ብድር ጫና ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ያለውን ምጣኔ ወደ 13 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የኢኮኖሚ እድገትን ከማሳላጡ ባሻገር ሦስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ይዞ መምጣቱንም ተናግረዋል።
በሸቀጦችና የአገልግሎት ወጪ ንግድ የተሻለ አፈጻጸም መኖሩንም ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
በሪፎርም ስራው በእዳ ውስጥ የነበሩ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስራ ወደ ትርፋማነት መሸጋገራቸውንም ገልጸዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት መንግስት ምንም ዓይነት ብድር ከብሔራዊ ባንክ አለመውሰዱን ጠቅሰው፤ ይህም የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት ትልቅ ፋይዳ ማበርከቱን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል መንግስት የኑሮ ውድነቱ በዜጎች ላይ ጫና እንዳያሳድር ለሴፍትኔት፣ ለመሰረታዊ ፍጆታ፣ ለነዳጅና ሌሎች ስትራቴጂክ ምርቶች የሚያደርገውን ድጎማ አጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል።
ለአብነትም ለአፈር ማዳበሪያ ብቻ 62 ቢሊዮን ብር ድጎማ መደረጉን ነው የተናገሩት ።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሀገር ውስጥ፣ በውጭ እና በርቀት የስራ እድል ፈጠራ ውጤታማ ስራ መከናወኑንም ሚኒስትሯ ባቀረቡት ሪፖርት ጠቅሰዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026