የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ለምርት ዘመኑ ወደ ሀገር ውስጥ ከ1 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ ማዳበሪያ ተጓጉዟል

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በ2017/18 የምርት ዘመንእስከ አሁንከ1 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን አስታወቀ።

መንግስት ለ2017/18 የምርት ዘመን ግብዓት የሚሆን 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን (24 ሚሊዮን ኩንታል)የአፈር ማዳበሪያ ገዝቶ ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት እቅድ ይዟል።


ከተያዘው እቅድ ውስጥ እስከ ሚያዚያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከ1 ሚሊዮን 34 ሺህ ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን ባለስልጣኑ ገልጿል።

39 ሺህ 764 ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ ላይ እንደሚገኝም አመልክቷል።

የዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያው በድንበር የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ እና በባቡርመጓጓዙን የባለስልጣኑ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.