ሀዋሳ፤ሚያዝያ 6/2017 (ኢዜአ) :- በሲዳማ ክልል ከ29 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ ፡፡
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት ከ32 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ29 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ማዘጋጀት ተችሏል፡፡
በ4 ሺህ 500 ሄክታር ላይ አዲስ ቡናን ለመትከል ከጥር ወር ጀምሮ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች መቆፈራቸውንና በያዝነው ወር ተከላው እንደሚጀመር ጠቅሰዋል፡፡
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለቡና ተክል አስፈላጊውን እንክብካቤ የማድረግ እንዲሁም ያረጁና ምርት የማይሰጡ ቡናዎችን በመጎንደልና ነቅሎ በአዲስ የመተካት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በጉንደላና ነቅሎ በመተካት ሥራ ባለፈው ዓመት 8 ሺህ ሄክታር ማሳ ማደስ እንደተቻለ የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፥ በዚህ ዓመት ደግሞ 11 ሺህ 500 ሄክታር ማሳ መታደሱን ገልጸዋል፡፡
ቡና ከሚሰጠው ጠቀሜታው አንጻር በልዩ ትኩረት እየለማ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ የአለታ ወንዶ ወረዳ አርሶ አደር እንዳሻው ዩሬ ለዘንድሮ 1 ሺህ 500 ችግኝ ለመትከል ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልፀዋል፡፡
አዲስ የሚተክሉት የቡና ችግኝ ዝርያቸው የተሻሻለ መሆኑን ጠቅሰው ከተተከለ በሁለት ዓመት ውስጥ ፍሬ መስጠት እንደሚጀምር አስረድተዋል፡፡
የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር አየለ ቡናራ፤ አምና 1 ሺህ 500 የቡና ችግኝ መትከላቸውን ገልፀው ዘንድሮሞ ከ 1 ሺህ 700 በላይ ችግኞችን ለመትከል የጉድጓድና ችግኝ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
ለሚተክሉት የቡና ችግኝ በቂ የሆነ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት እንደሚጠቀሙ የተናገሩት አርሶ አደር አየለ በመካከሉም የጥላ ዛፎችን እንደሚተክሉ አስረድተዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025