
ሚዛን አማን፤ሚያዚያ 9/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ36 ሺህ 600 ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ቡና፣ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አሥራት መኩሪያ፥ በክልሉ የቡናን ምርታማነት ለማሳደግ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግና የግብይት አቅርቦት ሥራን በማዘመን ውጤታማ ሥራ መከናወኑን ለኢዜአ ተናግረዋል።
በክልሉ በቡና ማሳ ከተሸፈነው ከ582 ሺህ ሄክታር በላይ የቡና ማሳ ጥራቱን የጠበቀ ምርት ከብክነት በፀዳ መንገድ ለማግኘት ለቡና አምራቹ ሥልጠና መሰጠቱንም ጠቁመዋል።
ከዚህም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ከታቀደው 67 ሺህ 800 ቶን የቡና ምርት ውስጥ ከ36 ሺህ 600 በላይ ቶን ቡና ለማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ለማዕከላዊ ገበያ ከቀረበ ቡና ውስጥ 10 ሺህ 700 ቶን የሚሆነው የታጠበ ሲሆን ከ25 ሺህ 900 ቶን በላይ የሚሆነው ያልታጠበ ቡና መሆኑንም አንስተዋል።
የቡና ምርቱን ለማዕከላዊ ገበያ ያቀረቡት በማህበርና በግል የተሰማሩ አልሚዎች መሆናቸውን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ አልሚዎቹ ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን ለማሳደግ እንዲሰሩ ድጋፍ መደረጉን ጠቁመዋል።
በክልሉ ሕገ ወጥ የቡና ንግድ በታቀደው መጠን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ እንዳይቀርብ ማድረጉን ጠቅሰው፣ በቀጣይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ችግሩን ለመፍታት ይሰራል ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026