አዲስ አበባ ፤ሚያዝያ 9/2017(ኢዜአ)፡- የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ስኬታማ ለማድረግ ሁሉም አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ሀገራዊ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ዛሬ ውይይት ተካሂዷል።
ውይይቱ በኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የተመራ ሲሆን፣ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሰመሬታ ሰዋሰው እንዲሁም የሚኒስቴሩና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በሪፖርቱ ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃና በገንዘብ ሚኒስቴር ዘርፍ የታቀዱ ዋና ዋና ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶችና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተካተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት መንግስት በማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ መሰረት የታክስ ገቢን በማሳደግ፣ ወጪን በመቆጣጠር፣ ውጤታማ የዕዳ ማሻሻያ ድርድር በማድረግ፣ የውጭ የልማት ትብብርን በማሳደግና ተቋማዊ ሪፎርምን በማጠናከር መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር እያደረገ ይገኛል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ስኬታማ ለማድረግ ሁሉም አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።
አሁን ባለው ተለዋዋጭ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ ውስጥ እንደ ሀገር ተጠናክሮ ለመውጣት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንዲሁም የወጪ ንግድና ገቢን የሚጨምሩ ተግባራት ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
አቶ መላኩ አክለውም፣ ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት ተገቢውን የመንግስት ገቢ በመሰብሰብና ወጪን በመቆጣጠር የሀገር ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ከማድረግ አኳያ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚና ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።
የኢንዱስትሪውን ዘርፍ በጋራ በመስራት የተሻለ የስራ ዕድል እና የሀብት መፍጠሪያ ማድረግ እንደሚገባ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025