
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፡- በውጭ ምንዛሬ ጨረታው አንድ ዶላር በአማካይ 131 ነጥብ 4961 ብር መሸጡን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገለጸ።
ባንኩ ዛሬ ያደረገውን የ70 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል።
አንድ ዶላር በአማካይ በ131 ነጥብ 4961 ብር መሸጡንና በጨረታው ላይ የተሳተፉ 26 ባንኮች የውጭ ምንዛሬውን መውሰዳቸውን ገልጿል።
በዛሬው ጨረታ በተሸጠው ዶላር የባንኮቹን 96 በመቶ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት/ጥያቄ በአጥጋቢ ሁኔታ ምላሽ መስጠት መቻሉን አመልክቷል።
ብሔራዊ ባንክ ቀጣይ የውጭ ምንዛሬ ጨረታውን ከሁለት ሳምንት በኋላ ያካሂዳል።

ባንኩ ጨረታው የሚያካሂድበት ቀን እና ሰዓት ጨረታው ከመካሄዱ ከአንድ ቀን በፊት አስቀድሞ እንደሚያሳውቅም ገልጿል።
ጨረታው በማዕከላዊ ባንክ እየተከማቸ ካለው የውጭ ምንዛሪ የተወሰነውን መጠን ለግሉ ዘርፍ ለማቅረብና የባንኩን የገንዘብ ፖሊሲ ዓላማ ለማሳካት እንደሚረዳ ተገልጿል።
በተጨማሪም ጨረታው የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማረጋጋትና ሪፎርሙ ከተጀመረ ወዲህ መሻሻል እያሳየ የመጣውን የውጭ ክፍያ ሚዛን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚያግዝም ነው ባንኩ ያመለከተው።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026