የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በጨረታው አንድ ዶላር በአማካይ ከ131 ብር በላይ ተሸጧል - ብሔራዊ ባንክ

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፡- በውጭ ምንዛሬ ጨረታው አንድ ዶላር በአማካይ 131 ነጥብ 4961 ብር መሸጡን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገለጸ።

ባንኩ ዛሬ ያደረገውን የ70 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል።

አንድ ዶላር በአማካይ በ131 ነጥብ 4961 ብር መሸጡንና በጨረታው ላይ የተሳተፉ 26 ባንኮች የውጭ ምንዛሬውን መውሰዳቸውን ገልጿል።

በዛሬው ጨረታ በተሸጠው ዶላር የባንኮቹን 96 በመቶ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት/ጥያቄ በአጥጋቢ ሁኔታ ምላሽ መስጠት መቻሉን አመልክቷል።

ብሔራዊ ባንክ ቀጣይ የውጭ ምንዛሬ ጨረታውን ከሁለት ሳምንት በኋላ ያካሂዳል።


ባንኩ ጨረታው የሚያካሂድበት ቀን እና ሰዓት ጨረታው ከመካሄዱ ከአንድ ቀን በፊት አስቀድሞ እንደሚያሳውቅም ገልጿል።

ጨረታው በማዕከላዊ ባንክ እየተከማቸ ካለው የውጭ ምንዛሪ የተወሰነውን መጠን ለግሉ ዘርፍ ለማቅረብና የባንኩን የገንዘብ ፖሊሲ ዓላማ ለማሳካት እንደሚረዳ ተገልጿል።

በተጨማሪም ጨረታው የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማረጋጋትና ሪፎርሙ ከተጀመረ ወዲህ መሻሻል እያሳየ የመጣውን የውጭ ክፍያ ሚዛን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚያግዝም ነው ባንኩ ያመለከተው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.