የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በአሶሳ ከተማ የተሻለ የበዓል ፍጆታ ቁሳቁስና የእርድ እንስሳት አቅርቦት አለ - ሸማቾች እና ነጋዴዎች

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ):- በአሶሳ ከተማ ለትንሳዔ በዓል የተሻለ የፍጆታ ቁሳቁስና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩን ሸማቾች እና ነጋዴዎች ተናገሩ።

ኢዜአ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአሶሳ ከተማ ያለውን የግብይት ሁኔታ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

በወቅቱ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች እና ነጋዴዎች እንደተናገሩት የፍጆታ ዕቃዎች እና የቁም እንስሳት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ እንዳለ ገልጸዋል።


ዱቄት፣ ዘይት እና ሌሎች ለበዓል ፍጆታ የሚውሉ ዕቃዎችን ሲሸምቱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሙሉ ዓለሙ እንዳሉት በዓልን ምክንያት በማድረግ የተሻለ አቅርቦት አለ ብለዋል።

ይለፉ አበዛ የተባሉ የአትክልት እና ፍራፍሬ ነጋዴ በበኩላቸው ሽንኩርት በአካባቢው በስፋት በመመረቱ አቅርቦት ላይ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።

በተመሳሳይ የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦትም በተሻለ ሁኔታ መኖሩንና መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ሸማቾች ተናግረዋል።


በአሶሳ ከተማ የቁም እንስሳት ገበያ ማዕከል ያገኘናቸው ሸማች አቶ ስሜነህ ተፈራ የእርድ ሰንጋዎች ከሌላው ጊዜ በተሻለ መግባቱንና ሰው እንደየፍላጎቱ ግብይት እየፈጸመ መሆኑን አንስተዋል።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አስር ኢብራሂም ነጋዴዎች የፍጆታ ዕቃዎችን በበቂ ሁኔታ እንዲያቀርቡ የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።

ህብረተሰቡ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በቀጥታ ከአምራቹ እንዲያገኝ በማድረግ የበዓል ገበያው የተረጋጋ እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል።


በቁም እንስሳት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች በእርባታ እና በማድለብ ስራ የተሰማሩ አካላት ምርታቸውን ወደ ገበያ እንዲያቀርቡ ተደርጓል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.