
አሶሳ፤ ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ):- በአሶሳ ከተማ ለትንሳዔ በዓል የተሻለ የፍጆታ ቁሳቁስና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩን ሸማቾች እና ነጋዴዎች ተናገሩ።
ኢዜአ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአሶሳ ከተማ ያለውን የግብይት ሁኔታ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
በወቅቱ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች እና ነጋዴዎች እንደተናገሩት የፍጆታ ዕቃዎች እና የቁም እንስሳት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ እንዳለ ገልጸዋል።

ዱቄት፣ ዘይት እና ሌሎች ለበዓል ፍጆታ የሚውሉ ዕቃዎችን ሲሸምቱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሙሉ ዓለሙ እንዳሉት በዓልን ምክንያት በማድረግ የተሻለ አቅርቦት አለ ብለዋል።
ይለፉ አበዛ የተባሉ የአትክልት እና ፍራፍሬ ነጋዴ በበኩላቸው ሽንኩርት በአካባቢው በስፋት በመመረቱ አቅርቦት ላይ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።
በተመሳሳይ የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦትም በተሻለ ሁኔታ መኖሩንና መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ሸማቾች ተናግረዋል።

በአሶሳ ከተማ የቁም እንስሳት ገበያ ማዕከል ያገኘናቸው ሸማች አቶ ስሜነህ ተፈራ የእርድ ሰንጋዎች ከሌላው ጊዜ በተሻለ መግባቱንና ሰው እንደየፍላጎቱ ግብይት እየፈጸመ መሆኑን አንስተዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አስር ኢብራሂም ነጋዴዎች የፍጆታ ዕቃዎችን በበቂ ሁኔታ እንዲያቀርቡ የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በቀጥታ ከአምራቹ እንዲያገኝ በማድረግ የበዓል ገበያው የተረጋጋ እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቁም እንስሳት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች በእርባታ እና በማድለብ ስራ የተሰማሩ አካላት ምርታቸውን ወደ ገበያ እንዲያቀርቡ ተደርጓል ነው ያሉት።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026