
ጅማ፤ሚያዚያ 12/2017 (ኢዜአ)፦የጅማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የግብርና ስራዎችን የሚያቀላጥፉ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ይፋ አደረገ።
የጅማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን መሀመድ አብደላ፤ ኮሌጁ በተለይም የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ ፈጠራዎች ላይ በማተኮር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ባልሆነባቸው አካባቢዎች አርሶ አደሮች በማንዋል የሚሰሩባቸው ቀላል ማሽነሪዎች መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።
የበቆሎ መፈልፈያ፣ እና የሩዝ መውቂያ፣ የመኖ መፍጫና ሌሎችም ቀላል ማሽነሪዎች ከኮሌጁ ፈጠራዎች መካከል መሆናቸውን ዲኑ ጠቅሰዋል።
እነዚህ ማሽኖች በፍጥነት ስራዎች እንዲጠናቀቁ በማድረግ የአርሶ አደሮችን ጊዜና ጉልበት ከመቆጠብም ባለፈ የምርት ብክነትን የሚያስቀሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በብዛት ከተመረቱ በኋላ ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የማቅረብ እቅድ መኖሩን ጠቁመው፥ የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ ፈጠራዎች ላይ በማተኮር የፈጠራ ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።
ከኮሌጁ መምህራን መካከል ዋሲሁን ደሳለኝ የፈጠራ ውጤቶቹ በተለይም ለአርሶ አደሩ አጋዥ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ ለአገልገሎት እንዲበቁ ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በቀጣይም የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ ቀላል ማሽነሪዎችን በመፍጠር የግብርና ስራዎችን ለማቅለል የሚያስችሉ ፈጠራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026