
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 124 የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለጸ።
የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የፕሮጀክቶች ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክተር ብሩክ ተሆነ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በመዲናዋ በርካታ ኢንቨስትመንትን የሚያበረታቱ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል።
በመዲናዋ ባለፉት ጥቂት አመታት የተገነቡ የኮሪደር፣ የቱሪዝም መሰረተ ልማቶችና መዳረሻዎች እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ኢንቨስትመንቱ እንዲያድግ እያስቻሉ ነው ብለዋል።
በከተማዋ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ በመሆኑም በተለይ በቱሪዝምና ሌሎች የአገልግሎት ዘርፎች ለመሰማራት በርካታ ባለሀብቶች ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ኮሚሽኑ ይህን ታሳቢ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍቃድ በተቀላጠፈ ሁኔታ ከመስጠት በተጨማሪ ፍቃድ የወሰዱ ባለሀብቶች በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን አንስተዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኮንስትራክሽን፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በአይሲቲ፣ በማኑፋክቸሪንግና በአገልግሎት ዘርፎች 124 ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶቹ ከአስር ሺህ በላይ ለሆኑ ነዋሪዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል፡፡
የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በፍጥነት ወደ ተግባር መግባት ለከተማዋ ኢኮኖሚ ትልቅ ሚና እየተወጣ መሆኑንም አንስተዋል።
እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፥ኮሚሽኑ አገልግሎቱን ለማዘመን ዲጂታላይዜሽን ላይ ውጤታማ ተግባራትን በማከናወን የኢንቨስትመንት ጉዳዮችን በቀላሉ በኦንላይን መፈጸም እንዲቻል አድርጓል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በማንሳት፥ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026