አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ በፍጥነትና በጥራት የተከናወኑ የልማት ስራዎች በፕሮጀክት አፈፃፀም ልምድ የሚወሰድባቸው መሆናቸውን በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን የጎበኙ የተለያዩ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ገለፁ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት የገንዘብ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግና በስሩ ያሉ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በመዲናዋ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝቷል።
ከጎበኟቸው የልማት ስራዎች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ትላንት የተመረቀው የካዛንቺስ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል፣ የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል፣ የገላን ጉራ የተቀናጀ የመኖሪያና የልማት መንደር እንዲሁም የጫካ ፕሮጀክት ይገኙበታል።
በዚሁ ጊዜ ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት ኑሪ ሁሴን በመዲናዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የከተማዋን ውበት ከማጉላት ባሻገር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን መገንዘባቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም አዲስ የስራ ባህልን ያሳደገ ልማት እንደሆነ ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ማከናወን እንደሚቻል ትምህርት የሚወሰድበት ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ቤዛዊት ግርማ በበኩላቸው የልማት ስራዎቹ ፕሮጀክቶች በአመራር ቁርጠኝነት በፍጥነትና በጥራት እንደሚጠናቀቁ ያረጋገጡ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።
ኮርፖሬሽኑ ከዚህ ልምድ በመውሰድ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ እና ሀብት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምክትል ስራ አስፈፃሚ ደመረ አሰፋ የልማት ስራዎቹ መዲናዋን ከማስዋብ ባሻገር ትምህርት በመውሰድ በተቋማቸው የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገድብ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ የግብርና እና የአግሮ ፕሮሰሲንግ የፖርትፎሊዮ ዳይሬክተር አስማ ረዲ የልማት ስራዎቹ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው ብለዋል።
የስራ ባህል በማሳደግ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት እና በጥራት ለማጠናቀቅ የተደረጉ ጥረቶች የሚደነቁ እና ትምህርት የሚወሰድባቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025