አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ የሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያ በድሮን ቴክኖሎጂ የገነባችውን አቅም አድንቋል።
በሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ኢንስፔክተር ጄኔራልና የደቡባዊ ዞን ጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሐመድ በሪድ የተመራ የልዑካን ቡድን የስካይ ዊን ኤሮናቲክስ ኢንደስትሪንና የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትን መጎብኘቱን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል፡፡
የአገልግሎቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በመርሐ-ግብሩ መሳተፋቸውንም ጠቁሟል፡፡
በጉብኝቱ የተሳተፉት የሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል የአቅም ግንባታ ዘርፍ ተወካይ ኮለኔል ሜጀር ሳልህ ኢዲን ሪዞኒ የስካይ ዊን ኤሮናቲክስ ኢንደስትሪን በመጎበኘታቸው መደሰታቸውንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በዘርፉ የደረሰችበት ደረጃ የሚደነቅ መሆኑንም ጨምረው መናገራቸው በመረጃው ተመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ በድሮን ቴክኖሎጂ የምታከናውናቸው ተግባራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ብሔራዊ ደኅንነትንና ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድ በተለያየ መልክ የሚገለጹ ፋይዳዎች እንዳሉትም ኮለኔል ሜጀር ሳልህ ኢዲን ሪዞኒ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያና የሞሮኮ የመረጃና የደኅንነት ተቋማት በተለያዩ መስኮች በትብብር ሢሰሩ መቆየታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መረጃ ጠቁሟል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025