
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ የሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያ በድሮን ቴክኖሎጂ የገነባችውን አቅም አድንቋል።
በሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ኢንስፔክተር ጄኔራልና የደቡባዊ ዞን ጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሐመድ በሪድ የተመራ የልዑካን ቡድን የስካይ ዊን ኤሮናቲክስ ኢንደስትሪንና የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትን መጎብኘቱን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል፡፡
የአገልግሎቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በመርሐ-ግብሩ መሳተፋቸውንም ጠቁሟል፡፡
በጉብኝቱ የተሳተፉት የሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል የአቅም ግንባታ ዘርፍ ተወካይ ኮለኔል ሜጀር ሳልህ ኢዲን ሪዞኒ የስካይ ዊን ኤሮናቲክስ ኢንደስትሪን በመጎበኘታቸው መደሰታቸውንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በዘርፉ የደረሰችበት ደረጃ የሚደነቅ መሆኑንም ጨምረው መናገራቸው በመረጃው ተመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ በድሮን ቴክኖሎጂ የምታከናውናቸው ተግባራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ብሔራዊ ደኅንነትንና ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድ በተለያየ መልክ የሚገለጹ ፋይዳዎች እንዳሉትም ኮለኔል ሜጀር ሳልህ ኢዲን ሪዞኒ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያና የሞሮኮ የመረጃና የደኅንነት ተቋማት በተለያዩ መስኮች በትብብር ሢሰሩ መቆየታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መረጃ ጠቁሟል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026