የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያ በድሮን ቴክኖሎጂ የገነባችውን አቅም አደነቀ

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ የሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያ በድሮን ቴክኖሎጂ የገነባችውን አቅም አድንቋል።

በሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል ኢንስፔክተር ጄኔራልና የደቡባዊ ዞን ጦር አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሐመድ በሪድ የተመራ የልዑካን ቡድን የስካይ ዊን ኤሮናቲክስ ኢንደስትሪንና የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትን መጎብኘቱን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል፡፡

የአገልግሎቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በመርሐ-ግብሩ መሳተፋቸውንም ጠቁሟል፡፡

በጉብኝቱ የተሳተፉት የሞሮኮ የሮያል ጦር ኃይል የአቅም ግንባታ ዘርፍ ተወካይ ኮለኔል ሜጀር ሳልህ ኢዲን ሪዞኒ የስካይ ዊን ኤሮናቲክስ ኢንደስትሪን በመጎበኘታቸው መደሰታቸውንም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በዘርፉ የደረሰችበት ደረጃ የሚደነቅ መሆኑንም ጨምረው መናገራቸው በመረጃው ተመላክቷል፡፡

ኢትዮጵያ በድሮን ቴክኖሎጂ የምታከናውናቸው ተግባራትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ብሔራዊ ደኅንነትንና ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድ በተለያየ መልክ የሚገለጹ ፋይዳዎች እንዳሉትም ኮለኔል ሜጀር ሳልህ ኢዲን ሪዞኒ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያና የሞሮኮ የመረጃና የደኅንነት ተቋማት በተለያዩ መስኮች በትብብር ሢሰሩ መቆየታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መረጃ ጠቁሟል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026