አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 26/2017 (ኢዜአ)፡-የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የዲጂታል ክህሎትን በማሳደግ በዘርፉ ተጨማሪ የአገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ የሚያደርግ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለፀ።
የ''አምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ ስልጠና ሐምሌ 2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
መርሃግብሩ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ዳታ ሳይንስና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲጨብጡ የሚያስችል ነው።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት ከመሰረተ ልማትና አስቻይ ስርዓት ከመዘርጋት በተጨማሪ የዲጂታል ክህሎት ያለው ማህበረሰብ አስፈላጊ ነው።
ስልጠናውን የተከታተሉ የመንግስት ሰራተኞች ለስራቸው ውጤታማነት እገዛ እያደረገላቸው መሆኑን ጠቁመው፥ አዳዲስ የስራ እድል መፍጠር የቻሉ እንዳሉም ተናግረዋል።
በተጨማሪም የዲጂታል ክህሎትን በማሳደግ በዘርፉ ተጨማሪ የአገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስትመንት እንዲመጣ ያደርጋል ብለዋል።
በመርሃግብሩ የሚሰጠው ስልጠና ከዲጂታል ክህሎት በተጨማሪ እውቀትን መሰረት ያደረገና ምክንያታዊ ውሳኔዎችን መስጠት የሚያስችሉ ክህሎቶችን ማግኘት የሚቻልበት እንደሆነም ተናግረዋል።
ስልጠናውን የተከታተሉ ወጣቶች በበኩላቸው ያገኙት ክህሎት ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውና ለስራቸው ተጨማሪ ክህሎትና እውቀት ያስጨበጣቸው መሆኑን ገልፀዋል።
ከሰልጣኞቹ መካከል ወጣት ዲቦራ የኔሰው እንዳለችው፥ ስልጠናው በነፃ የሚሰጥና ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ በመሆኑ ሁሉም እድሉን መጠቀም አለበት ብላለች።
ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ፅዮን ዘለቀ በበኩሏ፥ ስልጠናው ሳቢ በሆነ መልኩ የሚሰጥና ተጨማሪ የስራ እድልን ለማግኘትና ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ገልፃለች።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025