አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሌሎች የልማት ተግባራት የተመዘገቡ ስኬቶች በራስ አቅም መበልጸግ እንደሚቻል የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ምሁራን ገለጹ።
ከአገራዊ ለውጡ በኋላ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የልማት መርሃ ግብሮቸን በመቅረጽና ህዝብን በማስተባበር የተከናወኑ ተግባራት ለአዳዲስ ሥራዎች የሚያነሳሱ ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከስንዴ ምጽዋት ተላቃ ወደ ውጭ መላክ መጀመሯን ሲያበስሩ ባደረጉት ንግግር ታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ሲጀመሩ የሚጠናቀቁ የማይመስላቸው በርካታ እንደነበሩ ነው የተናገሩት።
በተለይም ኢትዮጵያ በስንዴ ራሷን ትችላለች ከራሷም አልፋ ለሌሎች ትተርፋለች ሲባል እውን የሚሆን ያልመሰላቸው እንደነበሩ አውስተዋል።
በአገሪቷ በህዝብ ቁጥርም ሆነ በተፈጥሮ ሃብት ያላትን እምቅ አቅም አሟጦ መጠቀም ከቻለች ከራሷ አልፎ ለሌሎች የሚተርፍ ጥሪት ማፍራት እንደሚቻል የሚያሳዩ መሆናቸውን ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ምሁራን ይናገራሉ።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ ለዚህ አብነት መሆኑን የሚጠቅሱት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የስርዓተ-ምህዳር መምህርና ተመራማሪ ቢቂላ ወርቅነህ (ዶ/ር) ናቸው።
ዶክተር ቢቂላ እንደገለጹት፤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ አሻራ ያረፈበት ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።
የግድቡ ግንባታ ኢትዮጵያውያን በተባበረ ክንድ በአንድነት መስራት የመቻላቸው ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ሌሎች ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ትምህርት የተወሰደበት መሆኑንም አንስተዋል።
የአገር አቀፉ አረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ብሄራዊ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ከፍተኛ በጀትና የሰው ሃይል የሚጠይቁ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል በተግባር የተረጋገጠበት መሆኑን ገልጸዋል።
ዶክተር አደፍርስ አረንጓዴ አሻራ እና የስንዴ ልማትን የመሳሰሉ የልማት ተግባራትም ህዝብን በማስተባበር ለዓለም ተምሳሌት የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደሚቻል ያረጋገጡ ተግባራት መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ምሁራኑ በቀጣይም የህብረተሰቡን አቅም በማስተባበርና በአግባቡ በመጠቀም ሌሎች የሀገሪቱን ጸጋዎች በማልማት ትልልቅ ስኬቶችን ማስመዝገብ እንደሚቻልም ብዙ ማሳያዎች እንዳሉ አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025