አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለማፋጠን የሴቶችን ተሳትፎ የበለጠ ማሳደግ እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለፁ።
6ኛው የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) ሴት ሥራ ፈጣሪዎች የንግድ ትርዒትና ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በንግድ ትርዒቱ መክፈቻ ላይ እንዳሉት፣ አፍሪካ በ2063 ለማሳካት ከያዘቻቸው አጀንዳዎች አንዱ የሴቶችን እኩልነትና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መሆኑን አንስተዋል።
የተቀናጀና የተናበበ ስራ ለአፍሪካ ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የኮሜሳ መስራች መሆኗን አንስተው፤ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ታደርጋለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለግሉ ዘርፍ ምቹ ሁኔታ የፈጠረና ተወዳዳሪነትን ያሳደገ መሆኑንም ተናግረዋል።
የአፍሪካን ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለማፋጠን የሴቶችን ተሳትፎ የበለጠ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸው፤ ኮሜሳ ለሴት ስራ ፈጣሪዎች እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኮሜሳ አባል ሀገራት ሴቶች በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።
የሚገጥማቸውን ፈተናዎች ተቋቁመው በንግድ ሥራ ውጤታማ የሆኑ ሴቶች በርካታ መሆናቸውንም ነው የጠቀሱት።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑንና በዘርፉ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለይታ ለመፍትሄው እየሰራች እንደሆነም ተናግረዋል።
የበለፀገች አፍሪካን እውን ለማድረግ የኮሜሳ አባል ሀገራት የበለጠ ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ፤ በአፍሪካውያን መካከል የሚደረገውን የንግድ ልውውጥ በማሳደግ የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ውህደት ማፋጠን ይገባል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት የሴቶችን እኩልነት ለማረጋገጥና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርፆ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025