አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎችን የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ገለጸ።
ባለሥልጣኑ ከህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ጋር በመተባበር የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የትብብርና የቅንጅት ስራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለስራቸው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ባለፉት ዓመታት በርካታ የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚህም የፖሊሲና ህግ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንና የተቋማት አቅም የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ይህንን ተከትሎ በተለይ ባለፉት የሪፎርም ዓመታት በርካታ ሲቪል ድርጅቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ ከስምንት ሺህ በላይ ድርጅቶች ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ሲሆን፤ 60 በመቶ የሚሆኑት ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተመዘገቡ መሆናቸወን ገልጸዋል።
እንደ አቶ ፋሲካው ገለጻ፤ የትብብር ስራዎችን በተደራጀ ስርዓትና በዘላቂነት ለማስቀጠል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከሚመለከታቸው ዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጋር የማቀናጀት ስራ እየተሰራ ነው ።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የትብብርና የቅንጅት መድረክ መቋቋሙንም አንስተዋል ።
ይህ ትብብር እና ቅንጅት የአገሪቷን ውስን ሀብት አጠቃቀም እንደሚያሻሽል፣የስራ መደራረብን እንደሚቀንስ እንዲሁም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያጎለብት ተናግረዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የፋይናንስ፣የአቅምና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎች የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አቶ ፋሲካው ሞላ አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ዋና እንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በበኩላቸው፥ የተቋሙ ስልጣንና ተግባር በተመለከተ ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለመፍታት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት ጉልህ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።
በጥናት፣በትምህርትና ስልጠና ስራዎች ላይም ከድርጅቶቹ ጋር በጋራ ለመስራት ያስችላል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025