
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎችን የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ገለጸ።
ባለሥልጣኑ ከህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ጋር በመተባበር የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የትብብርና የቅንጅት ስራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለስራቸው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ባለፉት ዓመታት በርካታ የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚህም የፖሊሲና ህግ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንና የተቋማት አቅም የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ይህንን ተከትሎ በተለይ ባለፉት የሪፎርም ዓመታት በርካታ ሲቪል ድርጅቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ ከስምንት ሺህ በላይ ድርጅቶች ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ሲሆን፤ 60 በመቶ የሚሆኑት ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተመዘገቡ መሆናቸወን ገልጸዋል።
እንደ አቶ ፋሲካው ገለጻ፤ የትብብር ስራዎችን በተደራጀ ስርዓትና በዘላቂነት ለማስቀጠል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከሚመለከታቸው ዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጋር የማቀናጀት ስራ እየተሰራ ነው ።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የትብብርና የቅንጅት መድረክ መቋቋሙንም አንስተዋል ።
ይህ ትብብር እና ቅንጅት የአገሪቷን ውስን ሀብት አጠቃቀም እንደሚያሻሽል፣የስራ መደራረብን እንደሚቀንስ እንዲሁም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያጎለብት ተናግረዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የፋይናንስ፣የአቅምና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎች የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አቶ ፋሲካው ሞላ አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ዋና እንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በበኩላቸው፥ የተቋሙ ስልጣንና ተግባር በተመለከተ ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለመፍታት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት ጉልህ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።
በጥናት፣በትምህርትና ስልጠና ስራዎች ላይም ከድርጅቶቹ ጋር በጋራ ለመስራት ያስችላል ነው ያሉት።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026