
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ተዋናዮች በጂኦፓርኮች እና ጂኦ ቱሪዝም ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ለዘርፉ እድገት ወሳኝ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ።
ቱሪዝም ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሣይንስና የባህል ድርጅት(ዩኔስኮ) ጋር "የዩኔስኮ ዓለም አቀፍ ጂኦፓርኮች እና ጂኦቱሪዝም ለዘላቂ ልማት ያላቸው ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የዩኔስኮ የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሸን እና የኢትዮጵያ ላይዘን ቢሮ ኃላፊ ሪታ ቢሶኖውት(ዶ/ር) እንዲሁም የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ የኢትዮጵያውያንና የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ባለሞያዎች ተገኝተዋል።
አውደ ጥናቱ በዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክስ እና ጂኦቱሪዝም ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን አቅም ማሳደግ ጨምሮ የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክ ፕሮጀክቶችን በኢትዮጵያ እና በሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማስጀመር ያለመ ነው።
በተጨማሪም የጂኦፓርክን ጽንሰ ሃሳብ በአህጉሪቱ ማስተዋወቅ ያለመ እንደሆነም ተገልጿል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ መንግሥት ትኩረት ከሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ አውታሮች አንዱ ቱሪዝም ነው።
ዘርፉ የሚጠበቅበትን ያህል ለሀገር እድገት እንዲያበረክት እየተመራ እንዳለ አንስተው፤ ይህም በተሰጠው ትኩረት ልክ ያሉ እድሎችን ለማዳበር እና ለማስተዋወቅ አስተዋጽኦ ፈጥሯል ነው ያሉት።
አዲሱ ረቂቅ የቱሪዝም ፖሊሲ የጂኦቅርስ ቦታዎችን መጠበቅ፣ ጂኦፓርኮችን ማቋቋም እና የጂኦቱሪዝም አስፈላጊነት ላይ ትኩረት የሰጠ ነው ብለዋል።
የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ተዋናዮችን በጂኦፓርኮች እና ጂኦቱሪዝም ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ለዘርፉ ዘላቂ ልማት ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
የዛሬው መድረክም የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክስ እና ጂኦቱሪዝም ጽንሰ ሀሳብን ለማስተዋወቅ ያግዛል ነው ያሉት።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026