
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ተዋናዮች በጂኦፓርኮች እና ጂኦ ቱሪዝም ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ለዘርፉ እድገት ወሳኝ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ።
ቱሪዝም ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሣይንስና የባህል ድርጅት(ዩኔስኮ) ጋር "የዩኔስኮ ዓለም አቀፍ ጂኦፓርኮች እና ጂኦቱሪዝም ለዘላቂ ልማት ያላቸው ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የዩኔስኮ የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሸን እና የኢትዮጵያ ላይዘን ቢሮ ኃላፊ ሪታ ቢሶኖውት(ዶ/ር) እንዲሁም የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ የኢትዮጵያውያንና የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ባለሞያዎች ተገኝተዋል።
አውደ ጥናቱ በዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክስ እና ጂኦቱሪዝም ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን አቅም ማሳደግ ጨምሮ የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክ ፕሮጀክቶችን በኢትዮጵያ እና በሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማስጀመር ያለመ ነው።
በተጨማሪም የጂኦፓርክን ጽንሰ ሃሳብ በአህጉሪቱ ማስተዋወቅ ያለመ እንደሆነም ተገልጿል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ መንግሥት ትኩረት ከሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ አውታሮች አንዱ ቱሪዝም ነው።
ዘርፉ የሚጠበቅበትን ያህል ለሀገር እድገት እንዲያበረክት እየተመራ እንዳለ አንስተው፤ ይህም በተሰጠው ትኩረት ልክ ያሉ እድሎችን ለማዳበር እና ለማስተዋወቅ አስተዋጽኦ ፈጥሯል ነው ያሉት።
አዲሱ ረቂቅ የቱሪዝም ፖሊሲ የጂኦቅርስ ቦታዎችን መጠበቅ፣ ጂኦፓርኮችን ማቋቋም እና የጂኦቱሪዝም አስፈላጊነት ላይ ትኩረት የሰጠ ነው ብለዋል።
የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ተዋናዮችን በጂኦፓርኮች እና ጂኦቱሪዝም ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ለዘርፉ ዘላቂ ልማት ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
የዛሬው መድረክም የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክስ እና ጂኦቱሪዝም ጽንሰ ሀሳብን ለማስተዋወቅ ያግዛል ነው ያሉት።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026