አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በወሰደቻቸው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማሳካት በትክክለኛ መንገድ ላይ እንደምትገኝ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ።
በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በፎረሙ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፥ ኢትዮጵያ በርካታ የለውጥ እርምጃዎች እየወሰደች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች እድገትን ለማስቀጠል፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እና መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳካት እንደሚያስችሉ አስረድተዋል።
ይህም ኢትዮጵያ በትክክለኛው የዕድገት ጎዳና ላይ እንድትገኝ አድርጓታል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፥ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ብሩህ ነው ብለዋል።
ለውጭ ባለሀብቶች ዝግ ሆነው የቆዩ ዘርፎችን የመክፈት ሀገራዊ ሪፎርም፣ የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎችና በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣታቸውን አንስተዋል።
የማበረታቻ ስርዓቶችም ባለሀብቶች ኢንቨስትመንታቸውን እንዲያስፋፉና ዘላቂነትን እንዲያረጋግጡ የሚያግዙ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ፎረሙ ኢትዮጵያ ያላትን የኢንቨስትመንት አቅም ለማሳየት ትልቅ ዕድል መሆኑን ጠቅሰው፥ የመድረኩ ተሳታፊዎችም የተሻሉ ልምዶችን እንዲለዋወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025