
ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የቴሌኮም ዘርፉ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።
ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ በደብረ ብርሃን ከተማ ለሀይለማሪያም ማሞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የኮምፒዩተርና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት፤ በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የቴሌኮም ዘርፉ እገዛና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህ ረገድ ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ ለትምህርት ቤቱ ላደረገው እገዛ ምስጋናቸውን አቅርበው የትምህርት ዘርፉን መደገፍ ለዲጅታል ዘርፉ እድገት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
የተደረገው ድጋፍ ዲጂታል ቴክኖሎጂን ለትምህርት ጥራትና ውጤታማነት በመጠቀም ወጣቶችን በእውቀትና ክህሎት አንጾ ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሪጅናል የውጭ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሲሳይ ዘሪሁን፤ ኩባንያው ለትምህርት ቤቱ የ14 ዘመናዊ ደስክ ቶፕ ኮምፒዩተሮች ድጋፍ ማድረጉን አንስተው ዓላማውም የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ እውቀትን ለተማሪዎች ተደራሽ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።

በእለቱ ለትምህርት ቤቱ ከተደረገው ድጋፍ በተጨማሪ በአካባቢው በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖችም የእህልና ሌሎችም ምግብ ነክ ቁሳቁሶችን መለገሱ ታውቋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026