
አሶሳ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን በብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ተናገሩ።
ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ በአሶሳ ከተማ እየተሰጠ ካለው የአመራሮች እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ስልጠና ጎን ለጎን በመደመር መጽሀፍ ገቢ እየተገነባ የሚገኘውን ሙዚየም፣ የአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ከጉብኝቱ በኋላም በመደመር መጽሀፍ እየተገነባ የሚገኘው ሙዚየም የክልሉን ህዝቦች ባህል እና እሴት የሚያንፀባርቅ እና ለትውልድ እንዲተላለፉ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል።
ፕሮጀክቱ የመደመርን ፅንሰ ሃሳብ በተግባር የሚያሳይ ለጥናት እና ምርምር የሚያገለግል የብልጽግና እሳቤ ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመሆኑም በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የግንባታ ሂደቱ 90 በመቶ የደርሰው ሙዚየሙ የቅርሶች ማስቀመጫ፣ ቤተመጻህፍት፣ ቴአትር ቤት እንዲሁም በክልሉ የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦች መገለጫዎችን የያዘ መሆኑን አንስተው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን ገጽታ የሚቀይር እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው ያሉት።
የኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አንስተው የከተሞች ዕድገት እና ዘመናዊነት ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ መሠረት የሚያኖር መሆኑንም ተናግረዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026