አሶሳ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን በብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ተናገሩ።
ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ በአሶሳ ከተማ እየተሰጠ ካለው የአመራሮች እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ስልጠና ጎን ለጎን በመደመር መጽሀፍ ገቢ እየተገነባ የሚገኘውን ሙዚየም፣ የአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ከጉብኝቱ በኋላም በመደመር መጽሀፍ እየተገነባ የሚገኘው ሙዚየም የክልሉን ህዝቦች ባህል እና እሴት የሚያንፀባርቅ እና ለትውልድ እንዲተላለፉ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል።
ፕሮጀክቱ የመደመርን ፅንሰ ሃሳብ በተግባር የሚያሳይ ለጥናት እና ምርምር የሚያገለግል የብልጽግና እሳቤ ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመሆኑም በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የግንባታ ሂደቱ 90 በመቶ የደርሰው ሙዚየሙ የቅርሶች ማስቀመጫ፣ ቤተመጻህፍት፣ ቴአትር ቤት እንዲሁም በክልሉ የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦች መገለጫዎችን የያዘ መሆኑን አንስተው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን ገጽታ የሚቀይር እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው ያሉት።
የኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አንስተው የከተሞች ዕድገት እና ዘመናዊነት ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ መሠረት የሚያኖር መሆኑንም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025