
አሶሳ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን በብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ተናገሩ።
ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ በአሶሳ ከተማ እየተሰጠ ካለው የአመራሮች እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ስልጠና ጎን ለጎን በመደመር መጽሀፍ ገቢ እየተገነባ የሚገኘውን ሙዚየም፣ የአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ከጉብኝቱ በኋላም በመደመር መጽሀፍ እየተገነባ የሚገኘው ሙዚየም የክልሉን ህዝቦች ባህል እና እሴት የሚያንፀባርቅ እና ለትውልድ እንዲተላለፉ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል።
ፕሮጀክቱ የመደመርን ፅንሰ ሃሳብ በተግባር የሚያሳይ ለጥናት እና ምርምር የሚያገለግል የብልጽግና እሳቤ ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመሆኑም በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የግንባታ ሂደቱ 90 በመቶ የደርሰው ሙዚየሙ የቅርሶች ማስቀመጫ፣ ቤተመጻህፍት፣ ቴአትር ቤት እንዲሁም በክልሉ የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦች መገለጫዎችን የያዘ መሆኑን አንስተው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን ገጽታ የሚቀይር እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው ያሉት።
የኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አንስተው የከተሞች ዕድገት እና ዘመናዊነት ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ መሠረት የሚያኖር መሆኑንም ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026