አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እየተገኙ ባሉ ውጤቶች ዓለም አቀፍ ድጋፍና ዕውቅና መገኘቱን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለጹ።
የኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ በፋይናንስ ዘርፍ የተደረጉ ማሻሻያዎችና የተገኙ ውጤቶችን በፎረሙ ላይ አቅርበዋል።
በፋይናንስ ዘርፍ የተደረገው ማሻሻያ መነሻ፣ የማሻሻያውን ይዘት፣ የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ የዘርፉን እቅድ በዝርዝር አቅርበዋል።
የውጭና የሀገር ውሰጥ የብድር ጫና መጨመር፣ የዋጋ ግሽበትና ሌሎች ያስከተሉት የማክሮ ኢኮኖሚ አለመጣጣም ለማሻሻያው መነሻ እንደሆኑ አስታውሰዋል።
በማሻሻያው ትኩረት ከተደረገባቸው ነጥቦች መካከል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ዘመናዊ ማዕከላዊ ባንክ የሚያደርጉ አሰራሮችን መዘርጋት፣ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር፣ የፋይናንስ መረጋጋትን ማምጣት ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል።
በማሻሻያው የፋይናንስ ዘርፉን በቴክኖሎጂ በመደገፍ አዳዲስ አሰራሮችና ገበያዎችን መፍጠር ተችሏል ነው ያሉት።
የውጭ ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰን መደረጉን ጠቅሰው፤ ለግል የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች ፈቃድ በመስጠት ወደ ስራ መግባታቸውንም አብራርተዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ የተመዘገቡ ውጤቶችን የዘረዘሩት የባንኩ ገዥ፤ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት መጨመር፣ የዋጋ ግሽበት መቀነስ፣ በፋይናንስ ዘርፉ መረጋጋት መታየቱ ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተዋል።
የባንክ ዘርፉን ለዓለም አቀፍ ተቋማት ክፍት ማድረግ፣ በባንኮች መካከል ያለው ግብይት መጨመር እና መንግስት ከብሔራዊ ባንክ የሚወስደውን ብድር ዜሮ ማድረስ መቻሉንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የተረጋጋ ምጣኔ ሃብት ለመፍጠር በወሰደችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና እየተገኙ ባሉ ውጤቶች ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ሀገራት ድጋፍና እውቅና እያገኘች መሆኑን ተናግረዋል።
ለአብነትም የዓለም የገንዘብ ድርጅት፣ የዓለም ባንክ፣ ከቻይናና ሌሎች ሀገራት የእዳ መክፈያ እፎይታ ጊዜና የገንዘብ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
የዲጂታል ፋይናንስ ክፍያ፣ ተቀማጭ የውጭ ምንዛሬ መጠን መጨመር፣ የፋይናንስ አካታችነትና ሌሎች ቀጣይ በፋይናንስ ዘርፉ ትኩረት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል መሆናቸውን ዘርዝረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025