
ነገሌ ቦረና፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦በምስራቅ ቦረና ዞን በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት 46 ኪሎ ሜትር የገጠር መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን የዞኑ መንገዶችና ሎጂስቲክስ ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
የጽህፈት ቤቱ ሀላፊ ተወካይ አቶ ዳግም ማንያዘዋል እንዳሉት፥ በበጀት ዓመቱ ባለፉት ወራት በዞኑ አምስት ወረዳዎች ከ124 ኪሎ ሜትር በላይ የገጠር ተደራሽ መንገዶች ግንባታ እየተካሄደ ነው፡፡
የመንገድ ግንባታዎቹም በዞኑ አሬሮ፣ ጉሚ ኤልደሎ፣ መዳ ወላቡ፣ ዋጭላና ምዕራብ ወላቡ ወረዳዎች መሆኑን ገልጸው፥ እስካሁን በጉሚ ኤልደሎ 20 ኪሎ ሜትር እንዲሁም በአሬሮ የ26 ኪሎ ሜትር መንገድ ግንባታ መጠናቀቁን ተናግረዋል።
ግንባታቸው ለተጠናቀቀው የመንገድ ፕሮጀክቶች ከ48 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ መደረጉንም አቶ ዳግም አስታውቀዋል፡፡
የገጠር መንገዶቹ ቀበሌን ከቀበሌ፤ ወረዳን ከቀበሌ እና ተጎራባች ወረዳዎችንና ዞኖችን እርስ በእርስ የሚያገናኙ መሆናቸውንም አክለዋል።
አጠቃላይ በግንባታ ላይ የሚገኙ መንገዶች ግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውል ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ከ239 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን ገልጸው፥ በሂደት ላይ ያሉ ግንባታዎችን ፈጥኖ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ምዕራብ ወላቡ ወረዳ የኦበርሶ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ተፈሪ ወንድሙ፤ በአካባቢያቸው ያለው መንገድ ምቹ ባለመሆኑ ምርታቸውን ወደ ገበያ ለማጓጓዝም ሆነ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት ለማግኘት ይቸገሩ እንደነበረ ተናግረዋል።
በአካባቢው የገጠር መንገድ ግንባታው በመጠናቀቁ የማርና የቡና ምርታቸውን በቀላሉ በመኪና አጓጉዘው ለገበያ ለማቅረብ እንደሚያግዛቸው ተስፋ አድርገዋል።
መንገዱ ወረዳችንን ከሌሎች ወረዳዎችና ከነገሌ ቦረና ዋና መንገድ ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ችግራችንን ያቃልላል ያሉት ነዋሪው የመንገዱ ግንባታ ፈጥኖ እንዲጠናቀቅ ድጋፍና ትብብራችን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የዚሁ ወረዳና ቀበሌ ነዋሪ ጎሳዬ በቀለ፤ ' የክልሉ መንግስት የማህበራዊ አገልግሎት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የገባውን ቃል በተግባር እየፈጸመ ነው ብለዋል፡፡
በመንገድ መሰረተ ልማት ረገድ በአካባቢያቸው አበረታች ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፥ ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎችም እንዲጠናከሩላቸው ጠይቀዋል።
#Ethiopian_News_Agency
#ኢዜአ
#ኢትዮጵያ
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026