አዲስ አበባ፤ግንቦት10 /2017 (ኢዜአ)፦መዲናዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ በአዲስ ዓለም ዓቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (ETEX 2025) ጎብኝተዋል።
ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት፤ ከተማዋ ከሀገር አልፎ የዓለም አቀፍ እና አህጉረ አቀፍ ኮንፈረንስ የማዘጋጀት አቅም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
ባለፉት አስር ቀናት ብቻ የኮንፈረንስ እና ኤክስፖዎች በመዲናዋ መከናወናቸውን ገልፀው፤ ይህም የከተማዋን ገቢ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
በሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ልማት ላይ ትልቅ ለውጥ እና እድገት እየተመዘገበ ይገኛልም ብለዋል።
ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
"ኢቴክስ 2025" ኤክስፖ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ጫፍ ላይ መድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ያዘጋጁት በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025