የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በቡና ግብይት ስንሰለት እና ምርታማነት ላይ የተሰራው ስራ የዘርፉን ገቢ አሳድጓል- የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦በቡና ግብይት ስንሰለት እና በምርታማነት እድገት ላይ በተሰሩ ስራዎች ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መቻሉን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ገለፁ።


በበጀት አመቱ 10 ወራት ወደ ውጭ ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ መንግስት የቡና ምርትና ምርታማነትን በመጨመርና ጥራቱን በማሻሻል በአለም ገበያ ተፎካካሪነትን ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው።


በዚህም በበጀት ዓመቱ አሥር ወራት 354 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 87 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡


ይህም በአገሪቱ የቡና የወጪ ንግድ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነ ከፍተኛ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት።


አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በመጠን 145 ሺህ ቶን ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸው፤ በገቢ ረገድም 870 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ የተመዘገበበት መሆኑንም ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።


ቡናን በስፋት መትከል፣ ያረጁ ቡናዎችን መጎንደልና ቡናን በብዛትና በጥራት ለማምረት አስችሏል ያሉት ዶክተር አዱኛ፤ በዚህም በሄክታር የሚገኘውን የቡና ምርት ማሳደግ መቻሉንና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር ላይ የተሰራው ስራ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ማስቻሉንም ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ የምታቀርበው የቡና ምርት ከአመት አመት በመጠንም በጥራትም እየጨመረ እንዲመጣ ማድረጉን ገልፀዋል።


በበጀት አመቱ ቀሪ ወራቶችም ከቡና ንግድ ለማግኘት የታቀደውን 2 ቢሊዮን ዶላር ከግብ ለማድረስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.