
አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦በቡና ግብይት ስንሰለት እና በምርታማነት እድገት ላይ በተሰሩ ስራዎች ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መቻሉን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ገለፁ።
በበጀት አመቱ 10 ወራት ወደ ውጭ ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ መንግስት የቡና ምርትና ምርታማነትን በመጨመርና ጥራቱን በማሻሻል በአለም ገበያ ተፎካካሪነትን ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው።
በዚህም በበጀት ዓመቱ አሥር ወራት 354 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 87 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡
ይህም በአገሪቱ የቡና የወጪ ንግድ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነ ከፍተኛ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት።
አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በመጠን 145 ሺህ ቶን ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸው፤ በገቢ ረገድም 870 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ የተመዘገበበት መሆኑንም ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።
ቡናን በስፋት መትከል፣ ያረጁ ቡናዎችን መጎንደልና ቡናን በብዛትና በጥራት ለማምረት አስችሏል ያሉት ዶክተር አዱኛ፤ በዚህም በሄክታር የሚገኘውን የቡና ምርት ማሳደግ መቻሉንና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር ላይ የተሰራው ስራ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ማስቻሉንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ የምታቀርበው የቡና ምርት ከአመት አመት በመጠንም በጥራትም እየጨመረ እንዲመጣ ማድረጉን ገልፀዋል።
በበጀት አመቱ ቀሪ ወራቶችም ከቡና ንግድ ለማግኘት የታቀደውን 2 ቢሊዮን ዶላር ከግብ ለማድረስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026