
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ ቦታ ወስደው ለዓመታት ሳያለሙ በቆዩ 96 ፕሮጀክቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።
የክልሉ መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ አጸደ አይዛ፥ በከተማዋ ለኢንቨስትመንት ተብለው የተወሰዱ ቦታዎችን ሳያለሙ ማስቀመጥ እንደማይቻልና አግባብ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
የክልሉ መንግስት የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ፈጥነው ወደ ሥራ እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል ያደርጋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ በክልሉ የወሰዱትን መሬት ሳያለሙ ለዓመታት አጥረው ባስቀመጡ 96 ፕሮጀክቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።
ከእነዚህም መካከል 34 ፕሮጀክቶች ውላቸው እንዲቋረጥ የተደረገ ሲሆን ቀሪዎቹ ላይ የማስጠንቀቂያ እርምጃ የተወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።
የጉብኝቱ ዓላማ የሪጂዮ ፖሊ ከተሞችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ለማሳደግ እና የባለሀብቶችን ጥያቄ ለመፍታት መሆኑን ገልፀው፥ ባለሀብቶች የሚያነሷቸውን ማነቆዎች በመፍታት ዘርፉን ለማነቃቃት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ በግብርናና በአገልግሎት እንዲሁም በኢንዱስትሪ ዘርፎች ከ1 ሺህ 700 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ስራ ላይ መሆናቸውንም ወይዘሮ አጸደ አመልክተዋል።
በክልሉ የኢንቨስትመንት ሥራዎችም ከ120 ሺህ በላይ ዜጉች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም ጠቁመዋል።
የክልሉ መንግስት እያከናወነ ያለውን የቁጥጥርና ክትትል እንዲሁም የድጋፍ ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፥ ባለሀብቶች የወሰዱትን መሬት በገቡት ውል መሰረት በማልማት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026