አዲስ አበባ፤ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 የቴክኖሎጂ ውጤቶቻቸውን ለማስተዋወቅና ትስስሮችን ለመፍጠር እንዳስቻላቸው የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ የፈጠራ ስራ አቅራቢዎች ተናገሩ፡፡
በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ለሶስት ቀናት በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በኢትዮጵያ መካሄዱ ይታወቃል፡፡
ኤክስፖው 2025 በዲጂታላይዜሽንና በቴክኖሎጂ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ማስተዋወቅና በርካታ ትስስር መፍጠሩም ተጠቁሟል።
በኤክስፖው በርካታ የሀገር ውስጥ፣ የውጭ ተቋማትና ግለሰቦች የቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡
በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራ አቅራቢዎች እንዳሉት፤ለአገር ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎች ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡
የኦሚሽቱ ጆይ ቴክ ቴክኖሎጂ መስራች መርዕድ ጉግሳ በኤክስፖው በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራን ማቅረባቸውን አንስተዋል፡፡
ቴክኖሎጂው አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀምና አፈርን በመመርመር ለየትኛው ዓይነት ሰብል ዝርያ እንደሚስማማ የሚለይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ይህም ምርታና ምርታማነትን ከማሳደግ አንጻር ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ጠቁመው፤ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎችም ሙከራ ተደርጎ ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የሚድራፍ ቴክኖሎጂ መስራችና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ራሔል ዘመነ በበኩላቸው፥ ሆስፒታሎችን እና ክሊኒኮችን ከፋርማሲዎች ጋር የሚያስተሳስር የፈጠራ ስራ በኤክስፖው መቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡
በዚህም ያቀረቡት ፈጠራ በዲጂታል (የኢ-መድኃኒት) ማዘዣ እና የዕቃ ዝርዝር አስተዳደር ስርዓቶችን የሚያዘምን መሆኑን ጠቅሰው፤ ፋርማሲዎች ያላቸውን የመድሃኒት ዓይነቶችና ብዛት የሚቆጣጠሩበት አሰራር ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡
በሌላ መልኩም የታካሚዎችን የመድሃኒት ማዘዣዎች መከታተልና የህክምና ታሪካቸውን መመልከት የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የዩቶጵያ ቴክኖሎጂ የማርኬቲንግ ክፍል ኃላፊ እምሻው ታፈሰ የአረንጓዴ ኢነርጂን ለማስፋፋት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡
በዚህም በአውቶሞቲቭና ግሪን ፈንድ እንዲሁም ፋይናንስን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳስሩ ስራዎችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለማስተዋወቅ ብሎም ትስስሮችን መፍጠር እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
ኤክስፖው ከሀገር ውስጥና ከውጭ ኩባንያዎች ጋር ትስስር ለመፍጠር ትልቅ ዕድል እንደፈጠረላቸው የገለጹት የፈጠራ ስራ አቅራቢዎቹ፥ ከፖሊሲ አውጪዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅት እንዲፈጥሩም እንዳስቻላቸው ገልጸዋል፡፡
በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በዲጂታላይዜሽን እና በቴክኖሎጂ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለዓለም ማስተዋወቅና በርካታ ትስስር መፍጠር ያስቻለ ነው፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025