የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ ለመኸር እርሻ ጥቅም ላይ የሚውል የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ እየተደረገ ነው - የክልሉ ግብርና ቢሮ

May 21, 2025

IDOPRESS

ግንቦት፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለመኸር እርሻ ጥቅም ላይ የሚውል የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮ ኃላፊው ጌቱ ገመቹ እንደገለጹት፣ ለመኸር እርሻ መደበኛ ኮምፖስትን ጨምሮ የተለያዩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ ለማዋል እየተሰራ ነው።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ የአፈር ለምነትን ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ጠቅሰው፣ በበጀት ዓመቱ 250 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ መደበኛ ኮምፖስት እና 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ቫርሚ ኮምፖስት ተዘጋጅቶ ለአርሶ አደሩ እየተሰረጨ ነው።


በክልሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጃ ማዕከላት በመገንባት አርሶ አደሩ በዝግጅት ሂደቱ ግንዛቤውን የማሳደግ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል።

በክልሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያን ከማዘጋጀት ጎን ለጎን የአርሶ አደሩን የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎትለሟሟላት በአሁኑ ወቅት ከ6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሉ ገብቶ ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑንም ገለጸዋል።


በቡኖ በዴሌ ዞን በተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጃ ማዕከል የአፈር ለምነት ባለሙያ መሃመድ ሱልጣን፤ ቫርሚ ኮምፖስት የአፈርን ለምነት በመጠበቅ፣ የአፈር አሲዳማነትን በመቀነስና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።

ማዕከሉ ቫርሚ ኮምፖስት በማምረት ለአርሶ አደሩ ከማቅረብ ጎን ለጎን አርሶ አደሮችን በማሰልጠን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በሚገኝ የቫርሚ ኮምፖስት ማምረቻ ማዕከል ውስጥ የምትሰራው ብርሃኔ ሶቦቅሳ፤ ማዕከሉ ቫርሚ ኮምፖስት አምርቶ በተመጣጣኝ ዋጋ ለአርሶ አደሮች እያቀረበ ይገኛል።

በተጨማሪ አርሶ አደሩ በራሱ በማምረት እንዴት መጠቀም እንደሚችል በማዕከሉ በኩል ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልጻለች።

የተፈጥሮ ማዳበሪያው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ከመጨመረ ባለፈ የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት የሚያወጣውን ወጪ ቀንሶለታልም ነው ያለችው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026