
ዲላ ፤ ግንቦት 12/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተሞችልማታዊ ሴፍቲኔቲ ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን ኑሮ እያሻሻለ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ገለጸ።
የፌደራልና የክልሉ አመራር አባላት በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ ልማታዊ የሴፍቲኔት ፕሮግራም እንቅስቃሴን በመስክ ተመልክተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ የምስራች ገመዴ በወቅቱ እንዳሉት፤ ልማታዊ የሴፍቲኔቲ ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ የከተሞችን ገጽታ እየቀየረ ነው።
በተለይ በገቢ ማስገኛ ስራዎች፣ በከተማ ውበትና ፅዳት የመጡ ለውጦችን ይበልጥ በማጠናከር ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚደረገውን ሂደት ለማፋጠን እየተሰራ ነው ብለዋል።
በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተሞች የምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔቲ ጽህፈት ቤት የዜጎች ተሳትፎና ሃብት ማፈላለግ ዴስክ ሃላፊ አቶ ሙሉዓለም ስሜ በበኩላቸው፤ ፕሮግራሙ በ87 ከተሞች ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ወገኖችን ተጠቃሚ በማድረግ ኑሯቸውን በዘላቂነት እንዲያሻሽሉ እያገዘ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ረገድ በዲላ ከተማ በአካባቢ ልማት የተሰማሩ ወገኖች ለራሳቸው ሃብት ከመፍጠራቸው ባለፈ የህብረተሰቡን ችግር እየፈቱ መሆናቸውን አንስተዋል።
ይህም የአካባቢ ልማት ስራን ቀጣይነት በማረጋገጥ ከተረጂነት መላቀቅ እንደሚቻል ማሳያ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ዴምሴ(ዶ/ር)፤ በከተማው የቀጥታ ድጋፋ ጨምሮ 2 ሺህ 141 የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች የፕሮግራሙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን ኑሮ በማሻሻል የስራና የቁጠባ ባህል ያሳደገ መሆኑን አንስተው፤ በዘርፉ የመጡ ለውጦችን ለማጠናከር የመስክ ምልከታው ድርሻ የጎላ ስለመሆኑም ነው ያመለከቱት።
ከተጠቃሚዎች መካከል ወይዘሮ ፀሐይ ክፍሌ በሰጡት አስተያየት፤ በልማታዊ ሴፍቲነት ባገኙት የገንዝብ ድጋፍና የክህሎት ስልጠና ታግዘው በንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት እራሳቸውን በመቻል ነግድው ያተረፉት ከ180 ሺህ ብር በላይ ተቀማጭ ገንዝብ እንዳላቸው ጠቅሰዋል።
በመስክ ምልከታው ከፌደራል፣ ከአለም ባንክ፣ ከክልልና ከተማ አስተዳደሩ የተወጣጡ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026