አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ለማብቃት ከብራዚል ጋር ተቀራርባ የምትሰራበት አቅጣጫ መቀመጡን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በብራዚል ሳኦ ፓውሎ ግዛት የሚገኙ የተለያዩ ኩባንያዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተን ስኬታማ ውይይቶችን አድርገናል ብለዋል።
የንግድ፣ ወታደራዊና የግብርና ዘርፍ የሚደግፉ አውሮፕላኖችን አምራች የሆነውን ኢምብሬር (Embraer) ኩባንያን ጎብኝተናል ያሉት አቶ ተመስገን ኩባንያው በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሀገራችን ከሚገኙ ተቋማት ጋር በትብብርና በጋራ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ተገንዝበናል ብለዋል።
የሳኦ ጆዜ ዶስ ካምፖስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ ሌላኛው ጉብኝት ያደረጉበት ተቋም መሆኑን ገልጸው የቴክኖሎጂ ፓርኩ የፈጠራ ሃሳብን ለለውጥና ችግር ፈች መፍትሄ በሚያመጡ ስታርት አፖች፣ መካከለኛና ከፍተኛ የተግባር ተኮር ስራዎች ዙሪያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተዘረጋ የዘርፉ ስራ ሂደት ያለው ተሳትፎ ሰፊ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይን ዕውን ለማድረግ በፈጠራና ቴክኖሎጂ የታገዘ ስራን መተግበር የጀመረችው ኢትዮጵያ ከመሰል ተቋማት ጋር በጋራ የመስራት መርህ ትከተላለች ብለዋል።
የብራዚሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ የኢትዮጵያ መንግስት ለቴክኖሎጂና ፈጠራ የሰጠውን ትኩረት አድንቋል ሲሉም ገልጸዋል።
በቀጣይ በቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ማብቃት ላይ ተቀራርበን የምንሰራባቸውን አቅጣጫዎች አስቀምጠናል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025