የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

​​​​​​​ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ለማብቃት ከብራዚል ጋር ተቀራርባ ትሰራለች - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ለማብቃት ከብራዚል ጋር ተቀራርባ የምትሰራበት አቅጣጫ መቀመጡን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በብራዚል ሳኦ ፓውሎ ግዛት የሚገኙ የተለያዩ ኩባንያዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተን ስኬታማ ውይይቶችን ‎አድርገናል ብለዋል።



‎የንግድ፣ ወታደራዊና የግብርና ዘርፍ የሚደግፉ አውሮፕላኖችን አምራች የሆነውን ኢምብሬር (Embraer) ኩባንያን ጎብኝተናል ያሉት አቶ ተመስገን ‎ኩባንያው በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሀገራችን ከሚገኙ ተቋማት ጋር በትብብርና በጋራ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ተገንዝበናል ብለዋል።



‎የሳኦ ጆዜ ዶስ ካምፖስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ ሌላኛው ጉብኝት ያደረጉበት ተቋም መሆኑን ገልጸው ‎የቴክኖሎጂ ፓርኩ የፈጠራ ሃሳብን ለለውጥና ችግር ፈች መፍትሄ በሚያመጡ ስታርት አፖች፣ መካከለኛና ከፍተኛ የተግባር ተኮር ስራዎች ዙሪያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተዘረጋ የዘርፉ ስራ ሂደት ያለው ተሳትፎ ሰፊ መሆኑን ጠቁመዋል።



‎ዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይን ዕውን ለማድረግ በፈጠራና ቴክኖሎጂ የታገዘ ስራን መተግበር የጀመረችው ኢትዮጵያ ከመሰል ተቋማት ጋር በጋራ የመስራት መርህ ትከተላለች ብለዋል።



‎የብራዚሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ የኢትዮጵያ መንግስት ለቴክኖሎጂና ፈጠራ የሰጠውን ትኩረት አድንቋል ሲሉም ገልጸዋል።

በቀጣይ በቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ማብቃት ላይ ተቀራርበን የምንሰራባቸውን አቅጣጫዎች አስቀምጠናል ብለዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.