
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ለማብቃት ከብራዚል ጋር ተቀራርባ የምትሰራበት አቅጣጫ መቀመጡን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በብራዚል ሳኦ ፓውሎ ግዛት የሚገኙ የተለያዩ ኩባንያዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተን ስኬታማ ውይይቶችን አድርገናል ብለዋል።
የንግድ፣ ወታደራዊና የግብርና ዘርፍ የሚደግፉ አውሮፕላኖችን አምራች የሆነውን ኢምብሬር (Embraer) ኩባንያን ጎብኝተናል ያሉት አቶ ተመስገን ኩባንያው በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሀገራችን ከሚገኙ ተቋማት ጋር በትብብርና በጋራ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ተገንዝበናል ብለዋል።

የሳኦ ጆዜ ዶስ ካምፖስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ ሌላኛው ጉብኝት ያደረጉበት ተቋም መሆኑን ገልጸው የቴክኖሎጂ ፓርኩ የፈጠራ ሃሳብን ለለውጥና ችግር ፈች መፍትሄ በሚያመጡ ስታርት አፖች፣ መካከለኛና ከፍተኛ የተግባር ተኮር ስራዎች ዙሪያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተዘረጋ የዘርፉ ስራ ሂደት ያለው ተሳትፎ ሰፊ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይን ዕውን ለማድረግ በፈጠራና ቴክኖሎጂ የታገዘ ስራን መተግበር የጀመረችው ኢትዮጵያ ከመሰል ተቋማት ጋር በጋራ የመስራት መርህ ትከተላለች ብለዋል።

የብራዚሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ የኢትዮጵያ መንግስት ለቴክኖሎጂና ፈጠራ የሰጠውን ትኩረት አድንቋል ሲሉም ገልጸዋል።
በቀጣይ በቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ማብቃት ላይ ተቀራርበን የምንሰራባቸውን አቅጣጫዎች አስቀምጠናል ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026