
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ለማብቃት ከብራዚል ጋር ተቀራርባ የምትሰራበት አቅጣጫ መቀመጡን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በብራዚል ሳኦ ፓውሎ ግዛት የሚገኙ የተለያዩ ኩባንያዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተን ስኬታማ ውይይቶችን አድርገናል ብለዋል።
የንግድ፣ ወታደራዊና የግብርና ዘርፍ የሚደግፉ አውሮፕላኖችን አምራች የሆነውን ኢምብሬር (Embraer) ኩባንያን ጎብኝተናል ያሉት አቶ ተመስገን ኩባንያው በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሀገራችን ከሚገኙ ተቋማት ጋር በትብብርና በጋራ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ተገንዝበናል ብለዋል።

የሳኦ ጆዜ ዶስ ካምፖስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ ሌላኛው ጉብኝት ያደረጉበት ተቋም መሆኑን ገልጸው የቴክኖሎጂ ፓርኩ የፈጠራ ሃሳብን ለለውጥና ችግር ፈች መፍትሄ በሚያመጡ ስታርት አፖች፣ መካከለኛና ከፍተኛ የተግባር ተኮር ስራዎች ዙሪያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተዘረጋ የዘርፉ ስራ ሂደት ያለው ተሳትፎ ሰፊ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ ርዕይን ዕውን ለማድረግ በፈጠራና ቴክኖሎጂ የታገዘ ስራን መተግበር የጀመረችው ኢትዮጵያ ከመሰል ተቋማት ጋር በጋራ የመስራት መርህ ትከተላለች ብለዋል።

የብራዚሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ፓርክ የኢትዮጵያ መንግስት ለቴክኖሎጂና ፈጠራ የሰጠውን ትኩረት አድንቋል ሲሉም ገልጸዋል።
በቀጣይ በቴክኖሎጂ ሽግግርና ባለሙያን ማብቃት ላይ ተቀራርበን የምንሰራባቸውን አቅጣጫዎች አስቀምጠናል ብለዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026