የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በአማራ ክልል የተገነቡ 151 ኢንዱስትሪ ዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል

May 26, 2025

IDOPRESS

ደብረ ብርሃን፤ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በመታገዝ በተከናወኑ ተግባራት ባለፉት አስር ወራት 151 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) አስታወቁ።


በደብረብርሃን ከተማ በአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ የተገነቡ ሶስት የአምራች ኢንዱስትሪዎች ዛሬ ተመርቀዋል።


በምረቃው መርሃ ግብር ላይ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብዱ ሁሴን(ዶር) እንደገለጹት፥ በክልሉ የሚከናወኑ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ተግባራተ አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ ነው።


ባለፉት አስር ወራት ብቻ "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" ንቅናቄ በመታገዝ 151 ኢንዱስትሪዎች ግንባታቸው ተጠናቆ ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን አስታውቀዋል።


ወደ ማምረት የተሸጋገሩትም 56 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል።


የተጀመረውን የኢንዱስትሪ ልማት አጠናክሮ ለማስቀጠል የክልሉ ህዝብና ባለሀብቱ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል።


በደብረ ብርሃን ከተማ ዛሬ የተመረቁት ኢንዱስትሪዎችም ከአርሶ አደሩ ጋር በማስተሳሰር በግብአት አቅርቦት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል።


የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፥በከተማዋ በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚሳተፉ ባለሀብቶች ቁጥር እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።


በዛሬው እለት ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በመገንባት ለምረቃ የበቁት ሶስት ፋብሪካዎችም ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል።


በቀጣይ የተጀመረውን ኢንዱስትራያላይዜሽን የበለጠ ለማስፋት በባለሀብቱ የሚነሱ የመልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።


የሀበሻ ፕላውድ ማን ፋክቸሪ ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ምህረት እንዳሉት፤በግማሽ ቢሊዮን ብር ወጪ የገነባው የእንጨት ውጤቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካ በቀን ተኪ ምርት በማምረት የውጪ ምንዛሬን ለማስቀረት የሚያግዝ ነው።


የዋን የማንፋክቸሪይግ ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ክንፈ በበኩላቸው፥ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ በመገንባት አሁን ላይ ከ100 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.