
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦ የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ መሆኑ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ገለጸ።
ሚኒስቴሩ ከከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የጭነት ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን የበለጠ ማቀላጠፍ በሚያስችል ጉዳይ ላይ በሞጆ ደረቅ ወደብ እየመከረ ይገኛል።
መድረኩ የሎጂስቲክስ ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተደራሽ በማድረግ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ የባለድርሻ አካላትን ሚና ለማጎልበት የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩን ጨምሮ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ነው።
ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ምርትንና አገልግሎትን ከቦታ ወደ ቦታ በማጓጓዝ በወቅቱ ለገበያ እንዲቀርብ በማድረግ በኩል ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026