
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦ የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ መሆኑ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ገለጸ።
ሚኒስቴሩ ከከባድ መኪና አሽከርካሪዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የጭነት ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን የበለጠ ማቀላጠፍ በሚያስችል ጉዳይ ላይ በሞጆ ደረቅ ወደብ እየመከረ ይገኛል።
መድረኩ የሎጂስቲክስ ስርዓቱን ቀልጣፋ እና ተደራሽ በማድረግ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ የባለድርሻ አካላትን ሚና ለማጎልበት የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩን ጨምሮ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ነው።
ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ምርትንና አገልግሎትን ከቦታ ወደ ቦታ በማጓጓዝ በወቅቱ ለገበያ እንዲቀርብ በማድረግ በኩል ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026